የትግራይ ክልል የገጠር መሬት የአካባቢ ጥበቃ አጠቃቀምና አስተዳደር ኤጀንሲ የፅህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳትና ጥቃቅን እቃዎች፣ የመኪና መለዋወጫ እቃዎችና የመኪና ጥገና ጋራዥ በ6 ወር የሚታደስ የአንድ አመት ውል ለማሰር ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ገጠር መሬት የኣካባቢ ጥበቃ ኣጠቃቀምና ኣስተዳደር ኤጀንሲ
  • የፅህፈት መሳሪያዎች፣
  • የጽዳትና ጥቃቅን እቃዎች፣
  • የመኪና መለዋወጫ እቃዎችና
  • የመኪና ጥገና ጋራዥ በ6 ወር የሚታደስ የአንድ አመት ውል ለማሰር ይፈልጋል፡


1 በዘርፉ የ2010/2011 ዓ.ም የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው

2 VATተመዝጋቢዎች መሆናቸው ማስረጃ የሚያቀርቡ

3 የሐምሌ/ነሐሴ 2010 ዓ.ም የቫት ዲክለራስዮን ያላቸውና ማስረጃ የሚያቀርቡ

4 ቲን ናምበር ያላቸውና ማስረጃ የሚያቀርቡ

5 በክልል ፋይናንስ ይሁን በፌዴራል የመንግስት ግዢ በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡና የ2010 ዓ.ም የታደሰ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት የሚያቀርቡ

6 ተጫራቾች የጨረታው ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ ለፅህፈት መሳሪያ፣የፅዳት እቃዎችና ጥቃቅን እቃዎች ብር 15000/አስራ አምስት ሺ ብር/ ለመኪና መለዋወጫ እቃዎች ብር 7000/ሰባት ሺ ብር/ ለመኪና ጥገና ጋራዥ ብር 4000/አራት ሺ ብር/በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ፣በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ ሌተር ኦፍ ክሬዲት በትግራይ ክልል ገጠር መሬት የአካባቢ ጥበቃ አጠቃቀምና አስተዳደር ኤጀንሲ ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝር መመሪያ ሰነድ የማይመለስብር 50/ሃምሳ/ብር በመክፈል ኤጀንሲው ከሚገኝበት አድራሻ ከ 2ተኛ ፎቅ በመውሰድ ዋጋ ማቅረቢያ ሰነዶቻቸው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከ18/01/2011 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 05/02/2011 ዓ.ም ድረስ በስራ ሰዓት ለክልሉ የገጠር መሬት የአካባቢ ጥበቃ አጠቃቀምና አስተዳደር ኤጀንሲ ፖ.ሳ.ቁ 1234 በአድራሻ በመላክ ወይም በግንባር በመቅረብ ኤጀንሲው በሚገኝበት ቦታ በ2ኛ ፎቅ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን በማስገባት መወዳደር ይችላሉ፡፡

7 ጨረታውበ18ኛው ቀን በ05/02/2011 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት ከታሸገ በኋላ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የተሻለ ቢሆንም ተጫራቾች ባይገኙም በተጠቀሰው መጨረሻ ቀንበ9፡00 ሰዓትበክልሉ የገጠር መሬት የአካባቢ ጥበቃ አጠቃቀምና አስተዳደር ኤጀንሲ ይከፈታል፡፡

8 አሸናፊዎች ላሸነፉት ንብረት ውል የማሰር /የመግባት/ግዴታ አለባቸው በገቡት ውል መሰረትም ይፈፅማሉ፡፡ በገቡት ውል ሳይፈፅሙ ቢቀሩ በእያንዳንዱ ቀን ካስያዙት የውል ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋ 0.001% በመቀጣት ገቢ እንዲያደርጉ ይደረጋል ወይም በህግ ይጠየቃል፡፡

9 ተጫራቾች በቀረበው የጨረታ ሰነድ አስተያየት/ጥያቄ ካለዎት ከጨረታ መክፈቻው ከ5 ቀን በፊት ማቅረብ ይችላሉ መጫረቻ ሰነዱ ስርዝ ድልዝ ካለበት የተሰረዘውን አይተም/ንብረት/ ተቀባይነት አይኖረውም ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ለሚመጣ ጥያቄ ኤጀንሲው መልስ ለመስጠት አይገደድም፡፡

10 ለመኪና ጥገና ጋራዥ ተወዳዳሪዎች ፋይናንሻል ዶክመንት ለብቻው ቴክኒካል ዶክመንት ለብቻው አሽገው ማቅረብ አለባቸው።

11 ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብታችን የተጠበቀ ነው፡፡

12 ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0344-417104 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo