በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ የጄኔሬተር መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የማሽነሪ መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የኮንስትራክሽን ማሽኖች፣ የብየዳ ዕቃዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የፈርኒቸር ዕቃዎች፣ የክችን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ
  • የጄኔሬተር መለዋወጫ ዕቃዎች
  • የማሽነሪ መለዋወጫ ዕቃዎች
  • የኮንስትራክሽን ማሽኖች
  • የብየዳ ዕቃዎች
  • የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች
  • የፈርኒቸር ዕቃዎች
  • የክችን እቃዎች

1 ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው የጨረታ አይነቶች ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው በአቅራቢነት ስለመመዝገባቸው የአቅራቢነት ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ።

2 የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ /ከፋይነት/ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ።

3 የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ።

4 ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው ለእያንዳንዱ ጨረታ የጨረታ ማስከበሪያ በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀው መመሪያ መሰረት በባንክ የተረጋገጠ CPO ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

5 ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ የዕቃውን አይነት ኤንቨሎፑ ላይ በግልፅ መፃፍ ይኖርባቸዋል።

6 የጨረታ ሰነዱን ከተጫራቾች ዝርዝር መመሪያ ጋር የማይመለስብር 200 በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታውጆ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ባሉት ቀናት ውስጥ ሽሬ እንደስላሴ በሚገኘው የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ግዥ ቡድን ቢሮ መግዛት ይቻላል።

7 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ሽሬ ከተማ በሚገኘው ማ/ዕዝ ጠ/መምሪያ መዝናኛ ክበብ ወስጥ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

8 ጨረታውጥቅምት 6 ቀን 2011 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 ሰዓትተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማ/ዕዝ መዝናኛ ክበብ ውስጥ ይከፈታል።

9 አሸናፊ ተጫራቾች ውል ሲፈፅሙ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ CPO ማስያዝ ይኖርባቸዋል። ያሸነፉበትን ዕቃ በራሳቸው ወጭ በማጓጓዝ እና በማራገፍ ሽሬ እንደስላሴ ከተማ በሚገኘው የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ግምጃ ቤት ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል።

10 መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ እንዲሁም 20% ጨምሮ ወይም ቀንሶ የመግዛት መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 034444 23 77/034 444 43 93 ይደውሉ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo