የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት የካልሲያም ሃይ/ክሎራይት፣ የሪኤጀንትና መለዋወጫዎች፣ኣልሙኒየም ሳልፌት ሃይድሬት፣ የውሃ ጥራት ላቦራቶሪ እቃዎችና እና መለዋወጫዎች ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል

የመቐለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት ጽህፈት ቤት

ሎት አንድ፦ የካልሲያም ሃይ/ክሎራይት  

ሎት ሁለት፦የሪኤጀንትና መለዋወጫዎች

ሎት ሦስት፦ ኣልሙኒየም ሳልፌት ሃይድሬት

ሎት አራት የውሃ ጥራት ላቦራቶሪ እቃዎችና እና መለዋወጫዎች

1. የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው፣
2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ፣
3. የጨረታው ዶክመንትየማይመለስ ለእያንዳንዱ ሎት ብር 200/ብር ሁለት መቶ/ በመክፈልመቐለ ውሃ አግልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክመንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ፤
4. የጨረታ ዶክመንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ30ኛው ቀን 2011 ዓ.ም 9፡00 ሰዓትወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ።
5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮበ30ኛው ቀን 2011 ዓ.ም 9:00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 9:30 ሰዓት ተጫራች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
6. ሁሉምተጫራቾች ለሎት አንድ 35,000፣ ለሎት ሁለት 30,000፣ ለሎት ሦስት 20,000፣ ለሎት አራት 30,000 የጨረታ ማስከበሪያ በCPO ፣በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና፣ በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና፣ ጥሬ ገንዘብ፣ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትእዛዝ፣ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
7. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት፤ በተጨማሪም በጨረታ ዶክመንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው።
8. በዶክመንቱ ከተሰጠው ስፔስፊኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም፡፡
9. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO፣ በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበርያ/ performance bond guarantee /10% ማስያዝ የሚችልና በ5 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክመንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል፣
10 .በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግስት ግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ
11. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክመንት ተቀባይነት የለውም።
12. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው።
13. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
14.የሚቀርበው ጨረታ ዶክመንትnቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዳሁም ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል።
15. ጽ/ቤቱ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ፦ትግራይ መቐለ ስልክ ቁጥር 034 440 7335 /0914755845 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo