የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋህዶ ቤተክስትያን የልማትና ክርስትያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን የትግራይ አህጉረ ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅ/ቤት በእንደርታ ወረዳ በማይ ኣምበሳ እና ደብረ ማዕርነት ቀበሌዎች በሚገኙ ሁለት ገዳማት እና ሁለት ትምህርት ቤቶች በድምሩ ከሁለት እስከ ኣራት መፀዳጃ ቤቶች ኣወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮምሽን የትግራይ አህጉረ ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅ/ቤት

በዚህም ከዚህ በታች የተዘርዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ የስራ ኣቋራጮችን እንዲወዳደሩ የጋብዛል።

1 ደረጃ 8 ፍቃድ የላቸው GC/BC የስረ ተቋራጮች

2 በተመሳሳይ የግንባታ ስራ በቂ ልምድ ማቅረብ የሚችሉ ይመረጣሉ

3 በዚህ ወቅት ከሰሩዋቸው የስራ ውሎች 70% ሰርተው ያጠናቀቁ

4 የ2010 ዓ/ም ግብር የከፈሉና የአመቱ ፈቃድ የሳደሱ

5 ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ የሆኑና ያለው ወር ተ.እ.ታ የከፈሉበት መረጃ ማቅረብ የሚችሉ

6 ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ 50 (ሃምሳ ብር) በመግዛት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 10 (ኣስር) ቀናት ውስጥ መግዛት ይቸላሉ።

7 ጨረታ ማስከበሪያ ብር 10000.00( ኣስር ሺ ብር) የባንክ ዋስትና ወይም ሲፒኦ በተለየ ፖስታ ኣሽገው ወይም በኣካል ይዘው መቅረብ የሚችሉ

8 የግንባታ የሳይት ርክክብ ከተመዘገበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 60 ቀናት ሙሉ በሙሉ ኣጠናቅቀው ማስረከብ የሚችሉ

9 ተሞልቶ የሚቀርበው የጨረታ ሰነድ ስርዝ ድልዝ ድል የሌለበት በድርጅታችን በተዘጋጀ ጨረታ ሰነድ ብቻ ተሞልቶ መቅረብ ኣለበት ይህንን ያላሟላ ተቋራጭ ከጨረታው ውጭ ይሆናል

10 የጨረታው ሰነድ ዋናውና ቅጅ ለየብቻው በሰም በተዘጋጀ ኢንቨሎፕ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ያስፈልጋል፣

11 የጨረታው ሳጥን 25/01/2011 ዓ/ም ከጧቱ 4:00 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጧቱ 4:30 ተጫራቾች ወይምህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወይም መገኘት የማይችሉ ከሆነ ሰነዶቹን በሟሟላት በፖስታው ላይ ይከፈትልኝ ብለው ከፈረሙና የድርጀታቸው ማህተም ካድርጉ በሌሉበት በትግራይ ኣህጉረ ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ይከፈታል።

12 ድርጅታችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታወን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo