ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለ2011 ዓ.ም በጀት ዓመት የትምህርት ዘመን የሚውሉ በጨረታ ቁጥር 06/2011 የተለያዩ እቃዎች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

Chereta yewetabet ken:Meskerem 15 2011 

በዚህ መሰረት፡- 

1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና ፍቃዱንም በዘመኑ የታደሰ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል

2. በቀረበው ዝርዝር ስፔሲፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችል

3. የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ምዝገባ ሰርተፊኬት 

4. ተጫራቹ TIN ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል

5. ለጨረታ ማስከበሪያ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስም እንደሚከተለው ማስያዝ የሚችል ይሆናል። • ሎት 1 የምግብ ግብአቶች ፡- 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺ ብር) • ሎት 2 የጤፍ ማስፈጨት ፡- 50,000 (አምሳ ሺ ብር ብቻ) 

6. ተጫራቾች የማቅረብያ /የአቅራቢ ሰርተፊኬት የተመዘገቡ መሆን አለባቸው። 

7. ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል በዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ከዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት ብሎክ 13 ቁጥር 7 መውሰድ የሚችል ሲሆን ዋጋው መቅረብ ያለበት ደግሞ ከዩኒቨርሲቲው የሚሸጥ ኦርጅናል የመምሪያ ሰነድ ማህተም ያለበት ዶክሜንት ማህተም የተጫራቹ በማድረግ ስርዝ ድልዝ የሌለው ዋጋ ብቻ ነው።

8. የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚሸጥ ይሆናል። 

9. ጨረታው ሳጥን የሚከፈትበት ቀን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመጨረሻ 16ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ4፡30 ሰዓትተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት በግልጽ ይከፈታል። 

10. ዝርዝር ስፔስፊኬሽን በድህረ ገጽ http://WWW.adu.edu.et ማግኘት ይቻላል። 

11. ዩኒቨርሲቲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። - ለበለጠ ማብራሪያ ፡- ስ.ቁ- 0344452318 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo