መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጂነሪንግ ሓ/የተ/የግ/ኩባንያ ኣውቶሞቲቭና እርሻ መሳሪያዎችና ቢዝነስ ዩኒት ንብረት የያዘ ባለ 40ና ፊት ኮንቴነር ከመቐለ ደረቅ ወደብ ወደ መቐለ ድህረ መሸጫ ግልጋሎት ማእከል እንዲሁም ባዶ ኮንቴነር ባለ 40ና ባለ 20 ፊት ከድህረ መሸጫ ግልጋሎት ማእከል ወደ መቐለ ደረቅ ወደብ ማጓጓዝ ስለፈለገ ከታች የተዘረዝሩትን መስፈርት የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ኩባንያችን ይጋብዛል።

መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

                                               የጨረታ መስፈርት

1 ተጫራቾች ቫት ተመዝጋቢ እና የ2010 ዓ/ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ እና የግብር መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ መሆን ኣለባቸው ።

2 ተጫራቶች የማይመለስ ኣንድ የታደሰ ንግደ ፍቃድና የግብር ምዝገባ ምስክር ወረቀት ፎቶ ኮፒ በማያያዝ የጨረታ ዋጋ በሰም በታሸገ ፖስታ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 18/01/2011ዓ/ም 6:00 ሰዓት መቐለ ድህረ ሽያጭ ኣገልግሎት ሳፕላይ መምርያ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።

3 የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 50 (ኣምሳ ብር) በመክፈል ከመቐለ ድህረ ሽያጭ ኣገልገሎት ሳፕላይ መምሪያ ዘወትር በስራ ሰዓት ከ 14/01/2011 ዓ/ም ጥዋት 2:00 ጀምሮ እስከ 18/01/2011ዓ/ም ከቀኑ 8:00 መውስድ ይቻላል።

4 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበረያ ሲፒኦ ብር 15000.00(ኣስራ ኣምስት ሺ ብር) በስም በታሸገ ፖስታ ማስገባት ኣለባቸው።በፖስታ ያልተሸገ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ተቀባይነት የለውም።

5 ጨረታ ሰነዱን ጨረታ ማስከብርያ ዋጋ ለየብቻው በታሸገ ፖስታ ማስገባት ኣለባቸው።

6 ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሦስተኛ ወገን ኣሳልፎ መስጠት ኣይችሉም።

7 ጨረታው 18/01/2011 ዓ/ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በዛው ዕለት 8:30 ታጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቐለ ድህረ ሽያጭ ኣገልግሎት ሳፕላይ መምሪያ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸው የተሟላ ከሆነ ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ ይከፈታል። ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት ጨምሮ መሆኑና ኣለመሆኑን በግልፅ መቀመጥ ኣለበት።

ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወስዳል።

8 ያስገቡት ዋጋ ስርዝ ድልዝ ከሆነ ተቀበይነት የለውም።

9 በጨረታው ያሸነፈ ለ 3 ወር ውል እንዲያስር ያደርጋል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo