ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የ4ኛ ደረጃ ሜንቴናንስ ሽሬ ኮርደር የተለያዩ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች የTOYOTA IHZJ 75፣ የTOYOTA IHZJ 76፣ የTOYOTA IHZJ 79፣የTOYOTA IHZ 79L ደብል ጋቢና፣ የTOYOTA IHZJ 105፣ የVOLVO FH12 380፣ የቢሾፍቱ ባስ መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የማሽን ሾፕ አላቂ ዕቃዎች፣ አላቂ የጋራዥ መሳሪያ ዕቃዎች፣ ቋሚ የጋራዥ መሣሪያ እቃዎች፣ የተሽከርካሪ ባትሪ እና የተሽከርካሪ ጎማ በግልጽ ጨረታ ግዥ ዘዴ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

በሀገር መከላኪያ ሚኒስቴር የ4ኛ ደረጃ ሜንቴናንስ ሽሬ ኮሪደር

ቁጥር 4ኛ ደ/ሜን/ሽ/ኮ 01/2011 ዓ.ም

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የ4ኛ ደረጃ ሜንቴናንስ ሽሬ ኮርደር በ2011 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን

• የተለያዩ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች የTOYOTA IHZJ 75፣

• የTOYOTA IHZJ 76፣ የTOYOTA IHZJ 79፣

• የTOYOTA IHZ 79L ደብል ጋቢና፣

• የTOYOTA IHZJ 105፣

• የVOLVO FH12 380፣

• የቢሾፍቱ ባስ መለዋወጫ ዕቃዎች፣

• የማሽን ሾፕ አላቂ ዕቃዎች፣

• አላቂ የጋራዥ መሳሪያ ዕቃዎች፣

• ቋሚ የጋራዥ መሣሪያ እቃዎች፣

• የተሽከርካሪ ባትሪ እና የተሽከርካሪ ጎማ በግልጽ ጨረታ ግዥ ዘዴ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራቾች በጨረታው ሊወዳደሩ ይችላል።

1. ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው የጨረታ ዓይነቶች፣ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በዕቃ አቅራቢነት ስለመመዝገባቸው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና የዘመኑን ግብር ስለመክፈላቸው ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።

2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ።

3. ተጫራቾች የሚጫረቱባቸውን ለእያንዳንዱ የጨረታ ማስከበሪያ በጨረታ ሰነድ ላይ በተገለጸው መመሪያ መሠረት በባንክ በተረጋገጠ የገንዘብ ማስያዣ (CPO) ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

4. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በሁለት ፖስታ ኦርጅናል እና ኮፒ በማድረግ የጨረታ ቁጥሩንና የዕቃውን ዓይነት በፖስታው ላይ በግልጽ መፃፍ ይኖርባቸዋል።

5. የጨረታው ሰነድ ከተጫራቾች ዝርዝር መመሪያ ጋር የማይመለስ 100 ብር (አንድ መቶ ብር ብቻ) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታውጆ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ባሉት የስራ ቀናት ውስጥ በ4ኛ ደረጃ ሜንቴናንስ ሽሬ ኮርደር ግዥ ቡድን ቢሮ መግዛት ይቻላል።

6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ሽሬ ከተማ በሚገኘው በማ/ዕዝ/ጠ/መምሪያ መዝናኛ ክበብ ውስጥ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

7. አሸናፊ ተጫራቾች ውሉን ሲፈርሙ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።

8. ያሸነፉበትን ዕቃ በራሳቸው ወጭ በማጓጓዝ በ4ኛ ደረጃ ሜንቴናንስ ሽሬ ኮርደር ግምጃ ቤት ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል።

9. ጨረታው በ18/01/2011 ዓ.ም ከረዳዱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ወኪሎቻቸው ህጋዊ የውክልና ወረቀት ይዘው መቅረብ አለባቸው።

10. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የ ጠተበቀ ነው።

- ለበለጠ መረጃ፡ -በስልክ ቁጥር 0344443083 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የ4ኛ ደረጃ ሜንቴናንስ ሽሬ ኮርደር

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo