የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2011 ዓ.ም በጀት አመት የሚያገለግል የተለያየ መጠን ያለው የውሃ ቆጣሪ ከነሙሉ መለዋወጫዎች አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ በጨረታው መሳተፍ ለምትፈልጉ ተጫራቾች ጥሪውን ያቀርባል።

የመቐለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት ጽህፈት ቤት

ጨረታ የወጣበት ቀን 2 /01 /2011 ዓም

1.

የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው። 

2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ። 

3. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ/ በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክሜንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ። 4. ጨረታ ዶክሜንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 2011 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ። 

5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ30ኛው ቀን 2011 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 

6. ሁሉም ተጫራቾች 120,000.00 የጨረታ ማስከበርያ በCPO, በሁኔታ ላይ ያልተሰመረተ የባንክ ዋስትና በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና ጥሬ ገንዘብ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትዕዛዝ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል። 

7. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው። 

8. በዶክሜንቱ ከተጠቀሰው ስፕስፍኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም። 

9. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበርያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበርያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ5 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክሜንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል። 

10. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግስት ግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንጽፍ 

11. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም። 

12. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው።

13. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንድ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው። 14. የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት 14.1 ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም።

14.2 ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል።

15. ጽ/ቤቱ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። አድራሻ ትግራይ መቐለ

መቐለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት

ስልክ ቁጥር 0344407335/0914755845

የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo