በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን ዕዝ ጠ/መምሪያ ለ2011 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ ለሠራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ መኪና ኪራይ፣ የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ቦቴ ኪራይ፣ የተለያዩ የህትመት ውጤቶች፣ አላቂ የጽሕፈት መሣሪያ፣ አላቂ የጽዳት ዕቃዎች፣ የተለያዩ የሲቪል አልባሳት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

መከላለያ ሰሜን ዕዝ ጠ/መምርያ

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2011

በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን ዕዝ ጠ/መምሪያ ለ2011 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተገለጹትን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

1. ለሠራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ መኪና ኪራይ

2. የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ቦቴ ኪራይ

3. የተለያዩ የህትመት ውጤቶች

4. አላቂ የጽሕፈት መሣሪያ

5. አላቂ የጽዳት ዕቃዎች

6. የተለያዩ የሲቪል አልባሳት

በዚህም መሠረት ለመኪና ሰርቪስ ኪራይ እና የፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ቦቴ ኪራይ በሥራው የተሰማሩ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ለሚያቀርቧቸው ሰርቪስ መኪናዎች ሙሉ ኢንሹራንስ የተገባላቸውና ስለመኪናቸው ከመንገድ ትራንስፖርት ዕውቅና ያገኙ የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ ባለንብረቶችን እና በተራ ቁጥር 3 ፣4፣ 5 እና 6 የተገለጹት የታደሰ ንግድ ፈቃድ ፣የግብር ከፋይ ሠርተፊኬት፣ የቫት ሠርትፊኬት እና የአቅራቢነት ምዝገባ ሠርተፊኬት ያላቸውን ይጋብዛል። ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መመሪያ እና ዝርዝር ሰነድ የያዘ ለተራ ቁጥር 1 እስከ 6 ለእያንዳንዳቸው 50.00/ ሃምሳ ብር/ በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት መቀሌ ኩሓ መንገድ እግሪ ወንበር አካባቢ ከሚገኘው የጠቅላይ መምሪያ ግዥ ቡድን ቢሮ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመግዛት በቢሮው ወደ ተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ጨረታው ሐምሌ 6/2010 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡ መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለተጨማሪ ማብራሪያ ስ.ቁ 0344-41-07-50

በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo