የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ የተለያዩ የኮምፒተርና ኮምፒዩተር ተዛማጅ ዕቃዎች እና ህትመት ሥራዎች ከህጋዊያን ነጋዴዋች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ትግራይ ክልል ጤና ቢሮ

1 ሎት 1 ኮምፒተርና ኮምፒዩተር ተዛማጅ እቃዎች 2 ሎት 2 የህትመት ሥራዎች 

1 የታደሰ ፈቃድ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN NO/ : የቫት ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የሚያዝያ ወር 2010 ዓም ቫት ዲክሌር ያደረገበትን እንዲሁም የታደሰ የኣቅራቢዎች ሰርተፌኬት ማቅረብ የሚችሉ 

2 የጨረታ ማስከበሪያ ሎት 1 የኮምፒተርና ኮምፒዩተር ተዛማጅ ዕቃዎች ስፒኦ ብር 30000 : ሎት 2 የህትመት ሥራዎች ስፒኦ 20000 ማስያዝ የሚችሉ 

3 ተወዳደራዎች ሎት 1 የኮምፒተርና ኮምፒዩተር ተዛማጅ ዕቃዎች የጨረታዉ ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ለእያንዳንዱ አንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ ዶክመንት እንዲሁም ሎት 2 የህትመት ሥራዎች አንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ ዶክመንት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዉስጥ በሥራ ሰዓት የግዥ ንኡስ ስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 42 ማስገባት የሚችል ሲሆን የሎት 1 ስፒኦ ኦርጅናል ቴክኒካል ደክመንት ላይ መታሸግ አለበት 

4 ጨረታዉ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተካታታይ ቀናይ የሚቆይ ሆኖ የመክፈቻ ቀን እና ሰዓት እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ የሆነ መመሪያዎች በሙሉ በሚሸጠዉ ሰነድ መመልከት ይቻላል

5 ተወዳዳሪዎች በተሰጠዉ ዝርዝር ስፔስፊኬሸን መሠረት የመወዳደሪያ ዋጋቸዉን መሙላት ይጠበቅባቸል

6 ተወዳዳሪዎች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት እና የትራንስፖርት እንዲሁም ሌሎች ወጪዎች ያካተተ መሆን አለበት ካልሆነ እንዳካተተ ይቆጠራል 

7 ተወዳዳሪዎች አኘናፊ ሆነዉ ከተገኙ ለሁሎቶም ሎቶች ዉል ከገቡበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር በ60 ተከታታይ ቀናት ማቅረብ ሲጠበቅባቸዉ በሎት 2 ዉስጥ የተካተቱ የመደበኛ በጀት የሆኑት የህትመት ሥራዎች ግን በ45 ተካታታይ ቀናት ማቅረብ አለባቸዉ 

8 የጨረታ ሰነዱ ዋጋ የማይመለስ ብር 100.00 ከፍለዉ ከክልል ትግራይ ጤና ቢሮ የግዥ ሣራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 42 በስራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ 

9 ቢሮዉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉ በሙለመ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ እንዲሁም 20% መጨምር አልያም መቀነስ ይችላል 

10 ማንኛዉም ግልፅ ያልሆነ ጥያቄ ካላችሁ የጨረታ ሰነድ የሚከፈትበት ቀን ከመድረሱ ከ 5 ቀናት በፊት በፅሑፍ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል 

11 ዋጋዉ ፀንቶ የሚቆየዉ /bid validity period/ 60 ቀናት ይሆናል 

12 በእያንዳንዱ ንብረት አሸናፊ ይለያል በድምር ወይም በጠቅላላ አሸናፊ አይደረግም ለበለጠ መረጀ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ ስቁ 0344404715 ደዉለዉ መጠየቅ ይችላሉ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo