በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ኮምፒዩተርና ፕሪንተር፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሙዚቃ መሳሪያዎች፣ ጄኔሬተርና ፓምፕ፣ የፈርኒቸር ዕቃዎች እና የኪችን ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ

1 ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸዉ የጨረታ አይነቶች ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸዉ በአቅራቢነት የምስክር በአገልግሎት ሰጪነት ስለመመዝገባቸዉ የአቅራቢነት ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና ግብር ስለመክፈላቸዉ ማረጋገጫ የሚችሉ

2 የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ /ከፋይነት/ ማርጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ

3 የንግድ ምዝገባና ምስክር ወረቀት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ

4 ተጫራቾች የሚጫረቱባቸዉን ለእያንዳንዱ ጨረታ የጨረታ ማስከበሪያ በጨረታ ሰነድ ላይ በተገለፀዉን መመሪያ መሰረት በባንክ የተረጋገጠ ስፒኦ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

5 ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ የእቃዉን ኣይነት ኤንቨሎፕ ላይ በግልፅ መፃፍ ይኖርባቸዋል

6 የጨረታ ሰነድ ከተጫራቾች ዝርዝር መመሪያ ጋር የማይመለስ ብር 200/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታዉጆ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ባሉት ቀናት ዉስጥ ሸሬ በሚገኘዉ የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መመሪያ ግዥ ቡድን ቢሮ መግዛት ይችላል

7 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸዉን ሽሬ ከተማ በሚገኘዉን ማ/ዕዝ ጠመምሪያ መዝናኛ ክበብ ዉስጥ ለዚሁ በተዘጋጀዉ ሣጥን ዉስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል

8 ጨረታዉ መጋቢት 20 ቀን 2010 ዓም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ማ/ዕዝ መዝናኛ ክበብ ዉስጥ ይከፈታል

9 አሸናፊ ተጫራቾች ዉል ሲፈፅሙ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ ስፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል ያሽፋቸዉን እቃዎች በራሳቸዉ ትራንስፖርት ወጭ በማጋጎዝ ሽሬ ከተማ በሚገኘዉ የማ/ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ግምጃ ቤት ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል

10 መሰሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ እንዲሁም ከአጠቃላይ ግዢ 20% ጨምሮ ወይም ቀንሶ የመግዛት መበቱ የተጠበቀ ነዉ

12 ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 034 444 23 77/ 034 444 43 93 ይደዉሉ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo