ድርጅታችን ማይጨዉ ፓርቲክል ቦርድ ፋብሪካ በፋብሪካዉ መጋዝን የሚገኙ ጥራት ያላቸዉ የሞራሌ ምርት ዉጤቶች እና የአትክልቶች ካሳዎች በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል

ማይጨው ፓርቲክል ቦርድ ኋ/የተ/የግ/ማህበር
  • ስለሆነም በጨረታ ለመሰተፍ የምትፈልጉ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸሁ የንግድ ማህበረሰብ ኣባላት ጨረታዉ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ በፋብሪካዉ ዋና መ/ቤት ከሚገኘዉ የፋይናንስ መምሪያ ቢሮ በመምጣትና በተጨማሪም መቀሌ ከሚገኘዉ ቀበሌ 16 ፎቶ ደሰታ ፊት ለፊት ከሚገኘዉ ቅ/ፅ/ቤታችን የንብረቶቹ ዝርዝር የያዘ ሰነድ በመዉስድ መጫረት የምትችሉ መሆነን እየገለፅን ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ያማሉ መሆን ይኖርባቸዋል

1 ተጫራቾች ህጋዊ የሆነ ንግድ ፋቃድ ያላቸዉና የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸዉ:: ለበለጠ የሰነድ ማረጋገጫቸዉን ኦርጅናል ኮፒ ማቅረብ አለባቸዉ

2 ለጨረታ የቀረቡትን ዕቃዎች መመልከት ለሚፈልጉ ተጫራቾች በፋብሪካዉ ቅጥር ግቢ በመገኙት ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 ተካታታይ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ቀርበዉ ማየት ይችላሉ

3 ንብረቱን ዝርዝር የያዘ ሰነድ ከፋብሪካችን ዋና መስሪያ ቤት ከፋይናንስ መምሪያ ወይም ቀበሌ 16 ፎቶ ደሰታ ፊት ለፊት ከሚገኘዉ ቅ/ፅ/ቤታችን ቀርበዉ የማይመለስ ብር 100 በመክፈል መዉስድ ይችላሉ

4 ተጫራቸች መግዛት የሚፈልጉትን ዕቃ ዋጋ በመግለፅ በታሸገ ፖስታ እስክ ህዳር 6/2010 ዓም 8:00 ሰዓት ድረስ በፋብሪካችን በመቅረብ ለጨረታ በተዘጋጀዉን ሳጥን ማስገባት አለባቸዉ

5 ጨረታዉ ህዳር 6/2010 ዓም ልክ 9:00 ሰዓት በፋብሪካችን ዋና መ/ቤት ሰፕላይ መምሪያ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይከፈታል

6 ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ በጥሬ ገንዝብ ወይም በስፒኦ ብር 10,000 ማስያዝ ይኖርባቸዋል

7 ተጫራቾች በጨረታ ያሸነፉትን ዕቃ ሙሉ ክፍያ በመፈፀም በ 5 ቀናት ወስጥ ማንሳት ይኖርባቸዋል :: በተጠቀሰዉ ጊዜ ገደብ ካላነሱ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙትን ገንዘብÂ በቅጣትÂ ለፋበሪካዉገቢ ተደርጎ አሸናፊነታቸዉ ይሰረዛል

8 ፋብሪካዉ ጨረታዉን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

9 ለበለጠ ማረጃ በስልክ ቁጥር ዋና ቢሮ 034 777 1259 መቀሌ ቅ/ፅ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo