የትግራይ ክልል የወጣቶች ስፖርት ጉዳዩች ቢሮ በ2010 ዓም ለስፖርት ዉድድር አገልግሎት የሚዉሉ የተለያዩ የስፖርት አይነት ትጥቆች የስፖርት እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ወጣቶች ማህበር

1 ዝርዝር የጨረታ ሰነድ ትግራይ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ቁጥር 23 100 መቶ ብር በመክፈል መዉሰድ ይቻላል

2 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 43000 በጥሬ ገንዘብ ወይም ከባንክ የተረጋገጠ ቼክ ወይም ስፒኦ ማስያዝ አለባቸዉ

3 ተጫራቾች ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸዉ የዘመኑ ግብር የከፈሉና ፈቃደቸዉን ያደሰ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና በየወሩ ለግብር ሰብሳቢ ኣካል የከፈሉ መሆናቸዉን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል በተጨማሪም የታደሰ የኣቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ

4 የጨረታ ሰነድ በኣማርኛ ቆንቆ የሚሞላ ሆኖ በግልፅ በሚነበብ ሁኔታ የተዘጋጀና ስርዝ ድልዝ የሌለበት መሆን ይኖርበታል

5 ተጫራቾች በማጭበርበር ወይም ከሙስና ጋር በተያያዘ ሁኔታ በኢትዩጰያ ህጎች የተደነገጉትን የሚያከብር መሆን እንዳለበት ይህ ሳይሆን ቢቀር በህግ ተጠያቂ መሆኑን

6 በጨረታ ሂደት ጨረታዉን ለማሰናከል ወይም ለማጭበርበር የሚሞክሩ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ተወርሶ ከጨረታ ዉጭ እንደሚሆኑ

7 ያሸነፉ ተጫራቾች የሚለዩት የተረከቡት ትክክለኛ ንብረቶች ለማቅረብ በሚያቀርቡት አነስተኛ ዋጋ ሆኖ ኣንድና ከኣንድ በላይ እቃዎች ላይ እኩል ዋጋ ያቀረቡ ተጫራቾች በእጣ የሚለዩ ይሆናል

8 የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሚያቀርበዉ ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ ያካተተ ወይም ያላካተተ መሆኑን በግልፅ ካስቀመጠ ተጨማሪ እሴት ታክስ አካቶ እንተሞላ ይቆጠራል

9 የጨረታ ሰነዱ ጨረታ ከወጣበት ቀን ከ 11/ 02/2010 ዓም እስከ 30/2/2010 ዓም በትግራይ ክልል ወጣቶች ስፖርት ቢሮ ቁጥር 23 በሥራ ሰዓት በመገኘት መዉሰድ የሚቻል መሆኑን በተመሳሳይ ግዜ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ የድርጅቱ ስም ፊርማ ማህተም በማስፈር ጨረታ ሳጥኑ ዉስጥ ማግባት ይቻላል

10 የጨረታ ሳጥን 30/2/2010 ዓም ሰዓት 8:00 ተዘግቶ 30/2/2010 ዓም 9:00 ሰዓት ይከፈታል ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት የሚከፈት መሆኑን ተወካዩች ተጫራቾች ባይገኙም ጨረታዉን ለመክፈት የሚያዳግት ነገር ኣይኖርመ

11 አሸናፊ ተጫራቾች አሸናፊነቱ ከተገለፀበት ጊዜ በሃላ ባሉት ሶስት ቀናት ዉስጥ ዉል ማሰር ይኖርበታል

12 አሸናፊዎች ተጫራቾች ያሸነፉባቸዉን እቃዎች ዉል ካሰረ በሃላ ባሉት 25 ቀናት ዉስጥ እቃዉ የትግራይ ክልል የወጣቶች ስፖርት ቢሮ መቀሌ ከተማ ባለዉ ጽቤት በራሱ ትራንስፖርት ኣቅርቦ የማስረከብ ግዴታ አለበት

13 ቢሮዉ በሚገዙት እቃዎች ላይ እንደ አስፈላጊነቱ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብት አለዉ

14 ዋጋዉ ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ጨረታዉ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ባሉት ቀጣይ 60 ቀናት ፀንቶ ይቆያል

15 ቢሮዉ የተሻላ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ ያለዉ መሆኑን

16 ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0344408877 በመደወል ወይም መቀሌ ከተማ በሚገኘዉ የትግራይ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ቁጥር 23 በኣካል በመገኘት መጠየቅ ይቻላል

ኣድራሻ የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ክልል ትግራይ ጉዳዮች ፊት ለፊት ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ ኮምፕሌክስ ህንፃ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo