አክሱም ዩኒቨርሲቲ ቀጥሎ የተገለፁትን፣ የእቃዎች አቅርቦት ግዥ ከህጋዊ ነጋዴዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ኣክሱም ዩኒቨርሲቲ

ጨረታ የወጣበት ቀን 24/ 01/ 2010 ዓም

.

የጨረታ ሰነድ ቁጥር (ሎት)

የጨረታ ዓይነት

የጨረታ ሰነድ መሸጫ ዋጋ

የጨረታ ማስከበሪያ

1

05

የምግብ ጥሬ እቃዎች እና አትክልቶች

100.00

100,000.00

2

06

የተለያዩ የኤሌክትሪክ እቃዎች

100.00

50,000.00

3

07

የተለያዩ የቧንቧ፣የህንፃ ጥገና እና ተዛማጅ እቃዎች

100.00

50,000.00

4

08

አላቂ የፅህፈት መሳርያ፣ የመማር ማስተማር እና አነስተኛ የቢሮ ቋሚ እቃዎች

100.00

50,000.00

5

09

አላቂ የፅዳት እቃዎች እና ተዛማጅ እቃዎች

100.00

50,000.00

6

10

ለምግብ ዝግጅት የሚያስፈልጉ የተለያዩ ቁሳቁሶች

100.00

50,000.00

7

11

ደረቅ የባህር ዛፍ እንጨት ለማገዶ የሚሆን

100.00

15,000.00

8

12

የተለያዩ የመኪና መለዋወጫ እቃዎች፣ የመኪና ጎማ እና ከላማደርያ

100.00

100,000.00

9

13

የመኪና የሞተር ዘይት እና ቅባቶች

100.00

10,000.00

10

14

ኦክስጅን ሲሊንደር

100.00

20,000.00

11

15

ንፁህ የመጠጥ ዉሃ በቦቴ

100.00

50,000.00

ስለዚህ፡-

1. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀንና ዓ.ም ጀምሮ ባሉትÂ 15 ተከታታይ ቀናትÂ በዩኒቨርሲቲው የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከግዥ ክፍል፣ህንፃ ቁጥር 53፣ቢሮ ቁጥር 002፣ዘወትር በሥራ ሰዓት ሰነዱ መውሰድ ይችላሉ።

2. ተጫራቾች በሥራው መስክ የተሰማሩና ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው መሆኑን የሚያስረዳና በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስፈልግ ማስረጃዎች ማያያዝ አለባቸው።

3. የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፣ የክልል/የፌዴራል በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ መሆን አለባቸው።

4. ለጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት 3% ልዩ አስተያየት ይደረጋል።

5. ጨረታው የሚከፈተው የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀንÂ 15 ቀን በኋላ ባለው ቀጣይ የሥራ ቀን ሆኖÂ በጨረታ ሰነዱ በተገለፀው ቀንና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት በግልፅ በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ይከፈታል።

6. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ሳይገኙ በመቅረታቸው የጨረታውን መከፈት አያስተጓጎልም።

7. የጨረታው አሸናፊ በጊዜው ቀርቦ ውል የማያስር ከሆነ በጨረታ ሰነዱ የተገለፀው ለጨረታ ማስከበሪያነት ያስያዘውን ገንዘብ አይመለስለትም።

8. ዩኒቨርሲቲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለተጨማሪ መረጃ፡_ በስልክ ቁጥር 034-775-35- 89/0913574560 ደውለው ይጠይቁ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo