የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2010 ዓ.ም በጀት ዓመት የሚያገለግል የተለያየ መጠን ያላቸው የውሃ ቆጣሪዎች (multi-jet Water meters,Cold flanged water Meter and their accessories.) አወዳድሮ በግልፅ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ ጨረታ ለመሳተፍ ለምትፈልጉ ተጫራቾች ጥሪውን ያቀርባል በዚህ መሰረት መጫረት የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-

የመቐለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት ጽህፈት ቤት

1.   የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ያላቸው።

2.   ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገና ቲን ቁጥር ያለው

3.   የጨረታው ዶክመንት የማይመለስ ለእያንዳንዱ ሎት 200 /ሁለት መቶ ብር/ መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክመንት ከደጋፊ ሥራ ሂደት ግዢ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 23 መግዛት ይችላሉ።

4.   ጨረታ ዶክመንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 2010 ዓ.ም 9፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ።

5.   ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 30ኛው ቀን 2010 . 900 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ 930 ሰዓት ተጫራች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።

6.   ሁሉም ተጫሪቾች 120,000/ ንድ መቶ ሃያ ሺ ብር/ የጨረታ ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ ዕውቅና ካለው ባንክ በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና (በCPO) በባንክ የተረጋገጠ ቼክ እና በሌተር ኦፍ ክሬዲት መልክ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።

7.   ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት። በተጨማሪም በጨረታ ዶክመንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው።

8.   በዶክመንቱ ከተሰጠው ስፔስፊኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም።

9.   የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO/በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ/ 10% ማስያዝ የሚችልና በ5 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክመንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል።

10. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግሥት ግዢ/ ሥራ/ እንዳይሳተፍ የሚያደርግ መሆኑ።

11. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክመንት ተቀባይነት የለውም።

12. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው።

13. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንዱ ነጠላ ዕቃ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።

14. ተጫራቾች አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ቴክኒካል እንዲሁም አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ፋይናንሻል የመጫረቻ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ አለባቸው።

15. ጽሕፈት ቤቱ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

16. አድራሻ፡- ትግራይ መቐለ ቀበሌ 03 መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 13

ስልክ ቁጥር፡- 251-0344-407335/6

ፋክስ 0344400911/0344410000

የመቐለ ውሃ አገልግሎት /ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo