የትግራይ ክልል መንገድ ሥራዎች ኢንተርፕራይዝ በ2010 በጀት ዓመት ለሚያከናዉናቸዉ የመንገድ ግንባታና ጥገና ሥራ አገልግሎት የሚዉሉ ኮንስተራክሽን ማቴሪያል ጎማ ባትሪ፣ ነዳጅ : ዘይትና ቅባት : የሰራተኞች ደንብ ልብስ :የፅዳት እቃዎች ፣ የፅሕፈት መሳሪያ እና አዘርስ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ትግራይ መንገድ ስራዎች ኢንተርፕራይዝ

ጨረታዉ የወጣበት ቀን--- 16/01/ 2010

ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን: በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 16ኛዉ ቀን

1 ተጫራቾች አግባብነት ያለዉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ : የቫት የምዝገባ የምስክር ወረቀት : የወቅቱን ግብር የከፈሉ መሆናቸዉ የሚያረጋግጥ ሰነድ የቲን ምዝገባ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል

2 የጨረታ ማስከበሪየ ዝርዝር በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለፀዉን መጠን በሲፒኦ ወይም አንኮንዲሽናል ጋረንቲ (unconditional Bank guarantee) ማስያዝ የሚችል

3 ተጫራቾች ዝርዝር የጨረታ ሰነድ ዘወትር በስራ ሰዓት ብር 50 በመክፈልና ከኢንተርፕራይዙ ግዥ ንብረት አሰተዳደር የስራ ሂደት መዉሰድ ይችላሉ

4 የጨረታዉ ሰነድ ዘወትር በስራ ሰዓት ለዚሁ በተዘጋጀዉ ሳጥን ማስገባት ወይም በፕ. ሳ .ቁ. 14 መላክ ይችላሉ

5 በጨረታዉ አሸናፊ የሆነዉ ተወዳዳሪ ማሸነፍ በደብዳቤ ከተገለፀበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 5 ቀናት በግንባር ቀርበዉ ዉል ማሰር አለባቸዉ

6 ጨረታዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛዉ ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ይከፈታል ይሁንና 16ኛ ቀን በዓል ከሆነ ወደሚቀጥለዉ የስራ ቀን ይተላለፋል

7 በጨረታዉ አከፋፈት ስነ ስርዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ ቢገኙ የመረጣል

8 ኢንተርፕራይዙ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታዉ በከፊልም ሆና ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0344416727 /0914734474 መጠየቅ ይቻላል

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo