የትግራይ ልማት ማሕበር በመደባይ ዛና ላዕላይ ማይጨዉ ታሕታሕ ማይጨዉ ሕንጣሎ ዋጅራት ወረዳዎች የትምህርትና የጤና ተቀሞች በአስራ ሁለት ሎቶች በመከፋፈል ማሰረት ይፈልጋል

የትግራይ ልምዓት ማሕበር

NB:ጨረታ የተለጠፈበት ቀን 08 /04/ 2009 ዓም

ደረጃቸው GC/BC-5 እና ከዝያ በላይ እና ከዝያ በላይ የሆኑ/ ተጫራቾችን ኣወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል

በዚህ መሰረት፦

1. የ2008 ዓ.ም የስራ ግብር የከፈሉ፣የንግድ ስራ ፈቃዳቸው ያሳደሱ፣በኮንስትራክሽን የአቅራቢነት፣የቫት፣ የቲን ሰርትፍኬትና የመጨረሻ ወር የቫት ዲክላሬሽን የሚያቀርቡ፣

2. በትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ የሚገኝ ዋና የስራ ሂደት ኮንስትራክሽን ቁጥጥርና ፍቃድ የተመዘገቡበት ሰርትፍኬት ወይ ደግሞ ከሌላ ክልል የምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፣

3. በማንኛውም ቦታ በግንባታ ሂደት ችግር ምክንያት ማስጠንቀቅያ ያልደረሰው ተቋራጭ የሆነ፣

4. የጨረታው ማስከበርያ ዋስትና በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው የታወቁ ባንኮች ለGC/BC-5ና ከዝያ በላይ 50,000.00 ( ሃምሳ ሺ ብር) በሲፒኦ ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣

5. ተጫራቾች ለሚሰሩት የህንፃ ፕሮጀክት ሳይት ከተረከቡበት ቀን ጀምሮ Â በ180/ አንድ መቶ ሰማንያ ተከታታይ ቀናት ኣጠናቆ ማስረከብ የሚችሉ፣

6. የጨረታው ዶክመንት ከ 30/ 03 /2009 ዓም ጀምሮ እስከ 21/ 04 /2009 ዓም ኣስፈላጊዉን ዶክመንት በመያዝ የማይመለስ ብር 500 (አምስትመቶ) በመክፈል ከትግራይ ልማት ማህበር ዋና ፅ/ቤት ቢሮ ቁጥር 435 መውሰድ ይችላሉ፣

7. የጨረታው ሰነድ በተጫራቾች መመርያ መሰረት ተሞልቶ ፣ቴክኒካልና ፋይናንሻል ዶክመንቶች ኦርጅናሉና ሁለት ፎቶ ኮፒዎች ፣ ሲፒኦ ለየብቻቸው በሰም ታሽጎው በአንድ ትልቅ ፖስታ ውስጥ ተከተውና በላዩ ላይ ለሚጫረቱት ፕሮጀክት ስም በሚታይ ቀለም ፅፈው በሁሉም ዶክመንት ላይ ተፈርሞበትና ህጋዊ የሆነ ማህተም በመምታት ይህ ማስታወቅያ ከወጣበት እስከ 21 04 2009 ዓም ከቀኑ 8:30 ሰዓት በትግራይ ልማት ማህበር ዋናው ፅ/ቤት ለዚሁ አገልግሎት የተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣

8. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት 21/ 04 /2009 ዓም ከቀኑ 8.30 የጨረታው ሳጥን ተዘግቶ በዛው ቀን 9:00 በተጠቀሰው ቀንና ቦታ ጨረታው ይከፈታል፣

አንድ ተጫራች ከሁለት ሎቶች በላይ ዶክመንት መግዛትም መወዳደርም አይችልም

ከትልማ ህንፃ ፕሮጀክት ወስዶ ይህ ጨረታ ሰነድ አየር ላይ እስከዋለበት ቀን ድረስ ፊዝካል አፈፃፀሙ ከ50% የሆነ ፕሮጀክት ያለዉ ተጫራች ከአንድ ሎት በላይ ዶክመንት መግዛትም ሆነ መወዳደር አይችልም

9. ኣሰሪው ፅ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው ኣይገደድም።

10. የመክፈቻው ቀን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆና በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል

11. ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፤-034-440-68-40 መጠየቅ ይቻላል

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo