ይመለከታል በመቐለ ዩኒቨርስቲ የህግና ሰነመንግስት ኮሌጅ ለኣካል ጉዳተኛ አገልግሎት ለሚዉል የአሌክትሪክ እቃዎች በዉስን ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

መቐለ ዩንቨርስቲ

ስለሆነም ከዚህ በታች የተጠቀሱት ዝርዝር የመወዳደሪያ መመሪያዎች መሰረት እንድትወዳደሩ እናስታዉቃለን

1 ተወዳዳሪዎች በዘረፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድና የግብር ከፋይ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸዉ

2 ተወዳዳሪዎች የ VAT የምስክር ወረቀት ማቅረብና የመወዳደሪያ ዋጋ VAT ጨምረዉ ዋጋዉ ማቅረብ አለባቸዉ

3 ተወዳዳሪዎች የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸዉ

4 ተወዳዳሪዎች በሚቀርቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ስማቸዉን : ፈርማቸዉና ሙሉ አድራሻቸዉ መግለፅ አለባቸዉ ::በተጨማሪም በፖስታዉ ላይ ሙሉ አድራሻ የጨረታ መለያ ቁጥር በመፃፍ ወደ ኮለጁ ገቢ ማድረግ አለባቸዉ

5 ተወዳዳሪዎች የታደሰ የንግድ ፍቃድ ኮፒ: የግብር ከፋይ ምስክር ወረቀት ኮፒ: የምዝገባ ምስክር ወረቀት የ VAT ምስክር ወረቀት ኮፒ ከመወዳደሪያ ዋጋቸዉ በሁለት በፖስታ ኦርጅናል እና ኮፒ በማለት አሽገዉ ማቅረብ አለባቸዉ

6 ተወዳደሪዎች ዉስን ጨረታዉ ከተከፈተ በኃላ ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሓሳብ ላይ ለዉጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግ አይችሉም

7 ጨረታዉ ለመዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታ ዉጭ እነደሚሆኑና ለወደፈት ጨረታ እንዳይሳተፉ ይደረጋል

8 የጨረታዉ ማስከበሪያ ከጠቅላላ የግዢ ዋጋ ብር 1059.20 (ኣንድ ሺ ኣምሳ ዘጠኝ ብር ከሃያ አምስት ብር ከጠና ሳንቲም) በመቀሌ ዩንቨርስቲ ህግና ስነመንግስት ኮሌጅ ስም C.P.O ማስያዝ አለባቸዉ

9 ተወዳደሪዎች የመወዳደሪያ ሃሳባቸዉ ከንግድ ምክር ቤት በወሰዱት የኮሌጅ ኦርጅናል ማህተም ያለበት የጨረታ ሰነድ ላይ መሆን አለበት በኮፒ ሞልቶ የሚያቀርብ ተወዳደሪ ከዉድድሩ ዉጪ ይሆናል

9 አሸናፊ ድርጅት ያሸነፈዉ እቃ በራሱ ወጪና ትራንስፖርት እቃዎች ወደ ዓዲሓቂ ካምፓስ ማድረስ አለበት

10 ተጫራቾች በድርጅታቸዉ ስም ቃለ መሃላ ፈርመዉ ማቅረብ ይኖርባችዋል

11 ኮሌጁ የሚገዛዉን እቃ ብዛት እንደ ኣስፈላጊነቱ እስክ 25% /ሃያ ኣምስት በመቶ/ መቀነስ ወይም መጨመር ይችላል

12 ጨረታዉ በሁለት ኢንቨሎፕ ታሽጎ የሚቀርብ ሲሆን ዋናዉና ቅጂ ሰነድ በድርጅቱ ስልጣን ባለዉ አካል ፊርማና ማህተም ሊኖረዉ ይገባል የንግድ ፍቃድ ኮፒ: የግብር ከፋይ ምስክር ወረቀት (TIN) ኮፒ :የኣቅረቢ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ኮፒÂ :VAT ምስክር ወረቀት ኮፒና CPO ከኦርጅናል ደኩመንት ጋር መግባት አለበት

13 ተጫራቾች በጨረታ ሰነድ ላይ የማብራርያ ወይም የማሻሻያ ጥያቄ ከተወሰነዉ ግዜ ገደብ በፊት በስልክ ቁጥር 0344408382 መጠየቅ ይችላሉ

14 ተጫራቾች በጨረታ የአፈፃፀም ሂደት ቅሬታ ካላቸዉ አቤቱታ የማቅረብ መብት አላቸዉ

16 ተመሳሳይ ዋጋ የቀረቡ ተጫራቾች በእጣ ይለያሉÂ Â

17 ጨረታዉ በአየር የሚቆይበት ግዜ ከጕንበት19/08 እስከ ሰኔ 03 /2008 ዓ/ም ሲሆን የሚዘጋበት ሰኔ 06 /2008 ዓ/ም ከጥዋቱ 3:30 ሲሆን የሚከፈትበት ደግሞ በዚሁ ቀን 4:00 ተጫራቾች ወይመ ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በመቀሌ ዩኒቨርሰቲ ዓዲ ሓቂ ካምፓስ ይከፈታል ሆኖም ተጫራቾች በራሳቸዉ ምርጫ ጨረታዉ በሚከፈተበት ግዜ ሳይገኙ በመቅረታቸዉ የጨረታዉ መከፈት አይስተጓጉሉም

18 ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo