የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ማይጨው ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ቤት ኪራይ በጨረታ ለሶስተኛ ጊዜ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

የሰሜን ሪጅን የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ማይጨው ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ቤት ኪራይ በጨረታ ለሶስተኛ ጊዜ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

በዚህ መሰረት፦

1. ቤቱ ሙሉ ግቢ ህንጻ ሁኖ 14 ክፍሎች ያሉትና (የእያንዳንዱ ክፍል ስፋት ቢያንስ 3*4) የሆነ ለደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት አመቺና ለዋና መንገድ ቅርብ የሆነ፣

2. የጽ/ቤቱ ሰራተኞች እና ተገልጋዮች ከሚያውኩ የድምጽ ብክለት የራቀ እንዲሁም አጎራባች ቤቶች እና ህንጻ ውስጥ የቢሮ አገልግሎቱን የሚያውኩ ሁኔታዎች የሌለው፣

3. የይዞታ ካርታ እና ዓመታዊ ግብር የተከፈለ መሆኑን ማስረጃ የሚያቀርብ፣

4. የራሱ የይዞታ ካርታ እና ዓመታዊ ግብር የተከፈለ መሆኑን ማስረጃ ያሚያቀርብ፣

5. የራሱ የሆነ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ የውሃና የስልክ መስመር ያለው፣

6. ለሚያከራየው ቤት የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ከሆነ በሚቀርበው ዋጋ ላይ ቫት ስለመካተቱ መግለጽ የሚኖርበት ሲሆን የኪራይ ቆይታ ጊዜው ለ3 ዓመት ውል መግባት ፈቃደኛ የሆነ፣

7. ከላይ የተዘረዝሩትን መስፈርት የምታሟሉ ህጋዊ ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን ሰነድ ከሰሜን ሪጅን ማይጨው ቅ/ጽ/ቤት ማህበራዊ ዋስትና ኣስተዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

8. ጨረታው የሚከፈተው ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ16 ተከታታይ ቀን ኣየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን እስከ 4፡00 ስዓት ድረስ በሰሜን ሪጅን ማይጨው ቅ/ጽ/ቤት በተዘጋጀው ሳጥን ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ መመለስ የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን። የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 100.00 ብር (አንድ መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላል እንዲሁም ጨረታው የሚከፈትበት ዕለት የዕረፍት ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የስራ ዕለት በተመሳሳይ ስዓት ጨረታው የሚከፈት መሆኑን እንገልጻለን።

ለቢሮ አገልግሎት የሚሆኑ ክፍሎችን ብዛት እና ስፋት በግልጽ በካሬ ሜትር፣ የአንድ ወርና የአንድ ዓመት ከፍያውን በማስላት በተዘጋጀው ሰንጠረዥ ውስጥ መግለጽ አለባቸው።

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 034 777 0289

የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የማይጨው ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo