የጨረታ ማስታወቅያ
ጨረታ ሰነድ ቁጥር 02/2024/2025
ትራንስ ኢትዮጵያ ኃ/የ/የግ/ማሕበር ለስልጠና ክፍል የሚያገለግሉ የተለያዩ መሳሪያዎች (Equipment and Special Tools) በግልዕ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለ ፈለገ በዘርፉ የተሰማራቹ ኣቅራቢዎች ከዚህ በታች የተገለፁ ነጥቦች የምታማሉ ተጫራቶች በጨረታዉ እንድትሳተፉ እንጠይቃለን።
1. ተጫራቶች በተጠቀሰው ዘርፍ የ2017 ዓ/ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ ኣለባቸው። የ2017 ዓ/ም ንግድ ፍቓድ ያላሳደሰ ተጫራች ከውድድሩ ውጪ ይሆናል።
2. ተጫራቶች የሚያቀርቡት ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ያካተተ ወይም ያላካተተ መሆኑን በግልፅ ማስቀመጥ ኣለባቸው፡፡ ይህ ካልተገለፀ የቀረበው ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (Vat) እንዳካተተ ተደርጎ ይወሰዳል።
3.ተጫራቶች የሚያቀርቡት ሰነድ ስርዝ ድልዝ ያለበት መሆን የለበትም። ስርዝ ድልዝ ያለበት ሰነድ ያቀረበ ተጫራች ከውድድሩ ውጭ ይሆናል።
4. ተጫራቶች ዋጋ መሙላት ያለባቸው ድርጅታችን በሰጣቸው ጨረታ ሰነድ ብቻ መሆን ኣለበት። ከዚያ ውጭ በራሳቸው ፕሮፎርማ ዋጋ የሞሉ ተጫራቶች ከውድድሩ ውጭ ይሆናሉ።
5. ተጫራቾች ነጠላ ዋጋና ድምር ዋጋ በጥንቃቄ መሙላት ኣለባቸው። ነጠላ ዋጋ ከተጠየቀው የዕቃ ብዛት (Quantity) ተባዝቶ ከሚመጣ ድምር ዋጋ ልዩነት ከተፈጠረ ነጠላ ዋጋው ትክክለኛ ተደርጎ ይወሰዳል።
6. ተጫራቶች ለጨረታ ማስከበርያ (Bid Bond) ባቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ 2% በትራንስ ኢያ ሓ/የተ/የግ/ ማሕበር ስም የተዘጋጀ ሲፒኦ ማስያዝ ኣለባቸው። ጠቅላላ ዋጋ ማለት ያቀረቡት የሁሉም ዕቃዎች ድምር ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (Vat) ጨምሮ ማለት ነው። የሚቀርብ ሲፒኦ ለብቻው ታሽጎ መቅረብ ኣለበት። ሲፒኦ ያላቀረበ ወይም በተጠቀሰው መጠን መሰረት ያላስያዘ ተጫራች ከውድድሩ ውጪ ይሆናል።
7. ኣሸናፊ የሆነ ተጫራች ላሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ (ተጫማሪ እሴት ታክስ ጨምሮ) ውል ማስከበርያ (Performance Bond) 10% ማስያዝ ኣለበት።
8. ተጫራቾች ፋይናንሻል ጨረታ ሰነድ በመቐለ በዳይሬክተር ግዢና የኣቅራቢዎች ትስስር ቢሮ እንዲሁም በአዲስ አበባ ሳሪስ ኣካባቢ በሚገኘው ትራንስ ታወር ላይዘን ኦፊስ የማይመለስ ብር 200 በመክፈል መውሰድ ኣለባቸው።
9. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ለ 60 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ መሆኑ ማወቅ ኣለባቸው።
10. ተጫራቶች ኣሸናፊ መሆናቸው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀን ውስጥ ውል ማስር ኣለባቸው።
11. ኣሸናፊ የሆኑ ተጫራቶች በአዲስ ኣበባ የተወዳደሩ ወይም በአዲስ አበባ ጨረታ ሰነድ ያስገቡ አዲስ አበባ በሚገኘው ላይዘን ኦፊስ፣ በመቐለ የተወዳደሩ ደግሞ መቐለ በሚገኘው ዋና ቢሮ ያሸነፉት ዕቃ ማቅረብ ኣለባቸው።
12. ተጫራቶች የጨረታ ሰነድ በታሸገ ፖስታ እስከ መጋቢት 09/2017 ዓ/ም ጠዋት ሰዓት 3:30 በመቐለ በዳይሬክተር ግዢና የኣቅራቢዎች ትስስር ቢሮና ኣዲስ ኣበባ ሳሪስ ኣካባቢ በሚገኘው ትራንስ ታወር ላይዘን ኦፊስ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ፋይናንሻል ፕሮፖዛል ኦርጅናልና ፎቶኮፒ ለየብቻ ማቅረብ ኣለባቸው።
13. ጨረታው መጋቢት 09/2017 ዓ/ም ጠዋት 3:30 ሰአት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ጠዋት 4:00 ሰአት በመቐለና በዳይሬክተር ግዢና የኣቅራቢዎች ትስስር ቢሮና ኣዲስ ኣበባ ሳሪስ ኣካባቢ በሚገኘው ትራንስ ታወር ላይዘን ኦፊስ ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
14. የጨረታ ሰነድ በተቀመጠው የጨረታ ማስታወቅያ መሰረት የተሟላ ከሆነ ተጫራቶች ባይገኙም ይከፈታል።
15. ድርጅታችን ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
16. ለተጨማሪ ማብራርያ ወይም ግልፅ ያልሆነላቸው ሃሳብ ተጫራቶች በኣካል በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 09 14 007 732/09 11 867 040 በስራ ሰዓት ደውላቹ መጠየቅ ትችላላቹ::