የጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ የመቐለ ወደብና ተርሚናል ቅ/ፅ/ቤታችን ለ2017 በጀት ከተያዘ የተርሚናል ጥገና ግብአት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለፈለገ፤ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የግብአት ዓይነቶች መስፈርቱን የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች በጨረታው እንድትወዳደሩ እንገልፃለን፡፡
ተቁ | የአገልግሎት ዓይነት | መለኪያ | ብዛት | የአንድ ዋጋ | ጠቅላላ ዋጋ | ምርመራ |
---|---|---|---|---|---|---|
1 | Selected.material (አንደኛ ደረጃ አፈር) | M3 | 320 |
1. ተወዳዳሪዎች ህጋዊ የታደስ ንግድ ፍታድ(2017ዓ/ም) ቀጥታ ተዛማች ዘርፍ ንግድ ያለው ፤ግብር ከፋይ
መለያ ቁጥር፣የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ስስ መክፈላቸው ማስረጃና የወሩ መጨረሻ ዲክላሬሽን ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ፅ/ቤት(ቢሮ) ማቅረብ የሚችሉ የምስክር ወረቀት ያላቸው ና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ ና ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
2. የሚያስገቡት ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆኑ መግለፅ አለበት።
3. በቴክኒክ ግምገማው ከ 70 በመቶ በላይ የቴክኒክ ውጤት ያገኘ ተጫራች ለፋይናንሻል ጨረታ ይወዳዴራል፡፡ተጫራቶች የፋይናንስ ፕሮፖዛል ሳይከፈት ወይም ያቀረበው እቃ በጥራቱ ለድርጅቱ አስፈላጊ ዝቅተኛ የቴክኒክ : መገምገሚያ - የያዙ ለተጫራቶች ውስጥ አንስተኛ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ከሆነ አሸናፊ ይሆናል፡፡ማሻሻያ ካላቸው የጨራታ የምን ከመዘጋቱ ከ 5 ቀናት በፊት የጨረታ ሰነድ ወደ ሚሸጥበት ቦታ በጽሁፍ ማቅረብ፤
4. ተጫራቶች በጨረታ ሰነዱ ግልጽ ያልሆነ ጉዳችን አስመልክቶ ጥያቄ ማብራርያ ወይም ማቅረብ አለባቸው፡፡
5. ተጫራቾች ማጭበርበርና ሙስናን በተመለከተ በትያ ህግ የተደነገጉትን ድንጋጌዎች የማክበር ግዴታ አለባቸው፡፡
6. የጨረታውን አካሄድ ለማዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታው ሊሰረዙ እንደሚችሉ ለወደፊትም በቅ/ጽ/ቤቱ ግዥ እንደማይሳተፉና ያስያዙት የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና በድርጅቱ ሊወረሱ እንደሚችሉ ማወቅ ይገባቸዋል፡፡
7. ጨረታው በአየር የሚቆይበት ግዜ ከ 07/06/2017 ዓ/ም እስከ 21/06/2017ዓ/ም ሲሆን የጨረታ ሳጥን የሚዘጋበት ቀን 21/06/2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 5:30 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን በ8፡00 ከሰዓት ይከፈታል፡፡
8. ተጫራቶች ለሚወዳደሩባቸው አገልግለቶች የጨረታ ማስረከብያ ዋስትና ከታወቀ ባንክ CPO ቢደ ቦንድ ብር 10,000.00 በመቐለ ወደብና ተርሚናል ስም ማስያ ይጠበቅባችዋል፡፡
9. ጨረታ ማስከበርያ ዋስትና ጨረታ ከተከፈተበትን ምሮ ለ 3 ቀናት ጸንቶ የሚቆይ ይሆናል፡
10. ጨረታ ማስከበርያ የሚመለሰው አሸናፊ ተራ ክስ በኋላ ነው፡፡
11. በውል አፈጻጸም ወቅት ዋጋ ማስተካከያ ማድረግ አይቻልም፡፡
12. የሚቀርበው የጨረታ ሰነድ በታሸገ ኢንቨሎፕ ሆኖ በፖስታው ላይ የተጫራቶች ስም ፣ አድራሻ የጨረታው ዓይነትና የአጫራች መስራቤት ስም መግለጽ አለበት፡፡
13. ተጫራቶች በጨረታ አፈጻጸም ሂደት ቅሬታ ካላቸው በ3 ቀን ውስጥ ቅሬታቸውን ለቅርንጫፍ የበላይ ሃላፊ በጽሁፍ የማቅረብና የማስማማት መብት አለባቸው፡፡
14. ተጫራቶች በሚያቀርቡት የጨረታ ማወዳደርያ ሰነድ ላይ ሙሉ ስማቸውን አድራሻቸው፤ ፈርማቸውና
የድርጅታቸው ማህተም ማስቀመጥ አለባቸው፡፡
15. ተጫራቶች የሚጫረቱበት ዋጋ በተዘጋጀው ሰነድ ብቻ ሞልተው ማቅረብ አለባቸው በጨረታ ሰነዱ ከተቀመጡ ዝርዝር አገልግሎትና መለኪያ ውጭ ማስቀመጥ ከውድርድር ውጭ ያድርጋል፡፡
16. ክፍያ የሚፈጸመው በቀጥታ በድርጅቱ በግዥ ፈጻሚ አካል ሆኖ ምን ግዜም ቢሆን በግዥ ውል በሚጠቅሱት የክፍያ ቃሎችና ሁኔታዎች መሰረት ይሆናል፡፡
17. ግዥ ፈጻሚ አካል 2% ዊዝሆልዲንግ በራሱ የሚሰበሰቡ መሆኑ ተጫራቶች ሊያውቁት ይገባል፡፡
18. በተጫራቶች የቀረበው ዋጋ የማይለወጥ ሲሆን ጨረታው : ከተከፈተ በኋላ ተጫራቶች ባቀረቡት የመወዳደርያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ራሳቸውን ከጨረታ ማግለል አይችሉም፡፡
19. በግምገማ ወቅት ሁለትና ከዛ በላይ የሆነ እጩ ተወዳዳሪዎች እኩል ዋጋ ሲያቀርቡ አሸናፊ ተጫራች በዕጣ እንዲለዩ ይደረጋል፡
20. የግምገማ ዘዴ መስፈርቶች የተጠየቀውን መስፈርት ያሟሉ ተጫራቶቸች አንስተኛ ዋጋ እና የእቃው ጥራት ታይቶ ለድርጅቱ አስፈላጊ ከሆነ ብቻ ይመረጣል።
21. አቅራቢው በሙሉ በተመለከተው ግዢ ውስጥ እቃውን አጠናቆ ካላስረከበ፣ ሳይፈጸም በቀረው የወጡ መጠን ላይ በየቀኑ 0.1 ፐርሰንት ወይም 1/1000ኛ መቀጫ ይከፈላል፡፡ አቅራቢው የውል ግዴታውን ሙሉ በሙሉ ካላጠናቀቀ ያስያዘው የውል ማስረከበረያ ሙሉ በሙሉ ይወረሳል።
22. ድርጅቱ የእቃው ብዛት ሊጨመር ወይም ሊቀነስ የሚችልበት ውል ከተፈራረሙ በፊት በጨረታ ሰነዱ ከተገለጸው የአቅርቦት መጠን ላይ እስከ 20 በሞቶ (20%) የተሰላው በእቃው ቁጥር ብዛት ነው
23. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡
24. ሰነዱ 100ብር በመክፈል ከመቀለ ወደብና ተርሚናል ቅ/ጽ/ቤት ፋናን ቁጥር 7 መውሰድ ይችላል፡፡
25. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0344403183/0914012515 /መደወል ይችላል፡፡