የፕሮፎርማ ማስታወቅያ(Shopping)
የመቀሌ ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ፅሕፈት ቤት ለመቀሌ ከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራምን ኣገልግሎት የሚዉሉ የተለያዩ የእጅ መሳርያ(Hand tools ) እቃዎች በፕሮፎርማ ኣወዳድሮ መግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መስፈርቶች የምታማሉ ነጋዴዎች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል ፡፡
ተፈላጊ መስፈርቶች
1. የዘመኑ የታደሰ ንግድ ስራ ፍቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ፣ የኣቅራቢነት ምዝገባ ሰርቲፊኬት ፣ የሻት ምዝገባ
ሰርቲፊኬት ፣ የቅርብ ወር ሻት ሪፖርት ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ ።
2. የመወዳደሪያ ሀሳቡ ከ 27/05/2017 ዓ/ም እስከ 06/06/2017 ዓ/ም ሰአት3:30 ለተጫራቾች ክፍት ሁኖ የሚቆይ ሲሆን በዚህ ቀን 3:30 ተዘግቶ 4:00 ሰዓት ቢሮ ቁጥር 033 ይከፈታል።
3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድንጨረታዉ ከወጣበት ቀን ጀሚሮ የማይመለስ ብር 200 ብር በመክፈል ከመቀሌ እቅድና
ፋይናንሰ ዕ/ፈት ከተማ ኣግኣዚ ኦፕሬሽን ህንፃ በመገኝዉ 1ኛ ፎቅ ቢሮቁጥር 033 መግዛት ይችላሉ።
4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና ብር 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)በCPO ፣ በጥሬ ገንዘብ ፣ወይም በባንክ ዋስትና
ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ኣለባቸው ። የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ጨረታው ከተከፈተበት ግዜ አንስቶ ለ15 ቀናት ይሆናል ::
5. የእቃዎች ማስረከብያ ቦታ በመስራቤታችን ግምጃ ቤት ሆኖ ማስረከብያ ግዜው ግዢው ከታዘዘበት ቀን ጀምሮ በ15 ቀናት ውስጥ ይሆናል ፡፡
6. ኣቅራቢዎች ጠቅላላ ዋጋውን በቁጥርና በፊደል መፃፍ ኣለባቸው ፡፡ በቁጥር እና በፊደል በተገለፀው የዋጋ መጠን መካከል
ኣለመጣጣም ካለ በፊደል የተገለፀው ተቀባይነት ይነረዋል ። በነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ መካከል ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋው ተቀባይነት ይኖረዋል፡፡
7. አቅራቢዎች በእያንዳንዱ የዕቃ ዝርዝር ማቅረብያ ሰንጠረዥ ውስጥ የዕቃውን ኣይነትና ብዛት ፣ ነጠላ ዋጋ ፣ እና ጠቅላላ
ዋጋውን መሙላት እንዲሁም ቀን ፣ ፊርማና የድርጅቱ ማህተም ማስፈር ይገባቸዋል ።
8. ለአሸናፊ ተጫራቾች ዕቃውን ሙሉ ለሙሉ በውለታ መሰረት ኣጠናቅቆ ማስገባቱና ማጠናቀቁ ከተረጋገጠ በኋላ ቢበዛ በ5ቀናት ውስጥ ሙሉ ክፍያ ይከፈለዋል ።
9. ተጨራቾች የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ታክስን የሚያካትትና የማያካትት መሆኑን መግለፅ አለበት ። ታክስን በትክክል ካልተገለፀ የቀረበው ዋጋ ታክስ እንዳካተተ ተቆጥሮ ውድድሩ ይካሄዳል ፡፡
10. አሸናፊ እቅራቢ የሚለየው ለተጠቀሱት ዕቃዎች በድምር እዕቃ ዝቅተኛ ዋጋ ኣቅራቢ ( LOT based) ይሆናል ፡፡
11. ግዢ ፈፃሚው መ/ቤት ከአሸናፊ ድርጅት ጋር ውለታ ከመፈራረሙ በፊት የዕቃዉን ጠቅላላ ብዛት እስከ 20% (ሃያ ፐርሰንት) ጨምሮ ወይም ቀንሶ መፈራረም ይችላል ፡፡
12. ማንኛውም ተጫራች ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰአት በፊት የዋጋ ማቅረቢያው ሰነዱን /የመወዳደርያ ሀሳብ / ማስገባት
ይኖርበታል ፡፡ ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰአት በኋላ የቀረበ የዋጋ ማቅረብያ ሰነድ /የመወዳደርያ ሀሳብ /ተቀባይነት የሌለው ሲሆን ኢንቨሎፑ ሳይከፈት ለተጫራቹ ተመላሽ እንዲሆን ይደረጋል።
ከሰላምታ ጋር
0344-406747/0344-408501/0344-406839