በመ/ቤቱ ተርሚናል ውስጥ ለቢሮ/ሱቅ የሚሆን ኣንድ ክፍል፣ ለዕቃ ማሽግያ እና ለኢትፎርመሽን ደስክ የሚሆን ባዶ ቦታ በጠረታ ለማከራየ ይፈልጋል

የኢትዮጰያ ኤርፖርቶች ድርጅት

ለሰወሰተኛ ጊዜ የወጣ ግልፅ ጨረታ ማስታወቅያ

በመቐለ ኣሉላ ኣባነጋ ዓለም ኣቀፍ ኤርፖርት ኣስተዳደር ተርሚናል ውስጥ ያሉት ለቢሮ ወይም ለሱቅ ኣገልግሎት የሚውል ክፍል እንዲሁም ለዕቃ ማሸግያ እና ለኢንፎርሜሽን ደስክ የሚሆን ባዶ ቦታ በጨረታ ኣወዳድሮ ለማከራየት ይፈልጋል። ማንኛውም ተጫራች በሚወዳደርበት የኣገልግሎት በዘርፍ የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያለው ንግድ ፍቃድ ከሌለው በኣሸነፋበት የኣገልግሎት ዘርፍ በኣድ ወር ጊዜ ውስጥ ከሚመለከተው የንግድ ፍቃድ ሰጪ ኣካል ፈቃድ ኣውጥቶ ማቅረብ የሚችል ተጫራች ይጋበዛል።


 

ስለሆነም በጨረታ ለመካፈል የሚፈልግ ማንኛው ድርጅት ወይም ግለሰብ መወዳደር የሚችል ሲሆን ለጨረታው የተዘጋጀውን ዝርዝር መግለጫ ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 20.00 በመክፈል ሰነዱን መውሰድ ይቻላል።

  1. የጨረታው ሰነድ ከጥር 7/2006 ዓ/ም እስከ ጥር 21/2006 ዓ/ም በመቐለ ኣሉላ ኣባነጋ ዓለም ኣቀፍ ኤርፖርትቢሮ ቁጥር 6 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።

  2. ተጫራቶች የጨረታ ማስከበርያ ቢድ ቦንድ በተመለከተ በጨረታ ሰነድ መመልከት ይቻላል።

  3. ጨረታው ጥር 21/2006 ዓ/ም ከጥዋቱ 4:00 ሰዓት የሚዘጋ ሲሆን በዕለቱ በ4:30 ጥዋት በተዘጋጀው መሰብሰብያ ኣዳራሽ ውስጥ ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታ ይከፈታል።

  4. ኣሸናፊው ድርጅት ወይም ግለሰብ ኣሸናፊነቱ ከተገለፀ በኋላ በሰስት የስራ ቀናት ጊዜ ውስጥ ውሉን መፈረምና ያሸነፈበትን የውሉ ዋጋ 10% ለውል ማስከበርያነት በሲፒኦ ወይም በባንክ ጋራነቱ ማስያዝ ኣለበት።

  5. ተጫራቶች የሚያቀርቡት የመጫረቻ ዋጋ ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ ያላካተተ መሆን ኣለበት።

  6. ድርጅቱ ሰለጨረታው ኣፈፃፀም የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

  7. የበለጠ ማብራርያ ወደ ኤርፖርቱ ኣስተዳደር 0344421102 ደውለው መጠየቅ ይችላለ።


 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo