የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ

ሎት 1 ጽሕፈት መሣሪያዎች

ሎት 2 የኤለክትሮኒክስ ዕቃዎች

ሎት 3 የእህል ሚዛን

ሎት 4 የቢሮ ዕቃዎች(ፈርኒቸር)

ሎት 5 ድንካኖች

በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል በመሆኑም በጨራታዉ ለመወዳደር የምትፈልጉ ሕጋዊ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታዉ እንድትወዳደሩ እየጋበዝን የተዘጋጀዉን ዶክመንት ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 100 በመክፈል ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮኣችን የዕቃ ግዥ ክፍል በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መዉሰድ የምትቹ መሆኑን እየገለጽን በጨረታዉ ለመሳተፍ የሚያስችላቹ ግዴታዎች ማለትም

  • የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርትፍኬት የ ቫት ሰርትፍኬት የግበር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) ያለፈዉ ወር ቫት ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት
  • ተጫራቾች የጨረታ መመሪያዉን በጥንቃቄ አይተዉ መወዳደር አለባቸዉ
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰዉን መጠን ገንዘብ በ ሲፒኦ አሰርተዉ ጨረታ ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ ይኖርባቸዋል
  • ቢሮአችን በጨረታዉ ከቀረበዉ የዕቃዎች ብዛት እስከ 15% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነዉ
  • ጨረታዉ ሚያዝያ 11 ቀን 2008 ዓም ከጠዋቱ በ 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያዉኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በቢሮአችን የዕቃ ግዠ ክፍል ይከፈታል
  • ቢሮአችን ስለጨረታዉ ሌላ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታዉ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ
  • ተለጨማሪ ማብራሪያ 034 4403663 ወይም 034 4404346

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo