ኢማጅን ዋን ዴይ ኢንተርናሽናል ኦርጋናይዜሽን /imagine 1 day/ በሂላሪና ጋለን የገንዘብ ድጋፍ አገልግሎት በሚሰጥባቸው ፕሮጄክት አካባቢዎች ለሚግኙ ትምህርት ቤቶች ግብኣት የሚዉል የተማሪዎች መቀመጫ ዴስክ (combined desk) እና ጥቁር ሰሌዳ (Black board ) በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

ኢማጂን ዋን ዴይ ኢንተርናሽናል ኦርጋናይዜሽን

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

ኢማጅን ዋን ዴይ ኢንተርናሽናል ኦርጋናይዜሽን /imagine1day/ የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ የውጭ በጎ አድራጎት ድርጅት በኦሮሚያ፣ አማራ፣ትግራይ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፣ አፋር ክልል እና በደቡብ ክልል በትምህርት ጥራት ማሻሻል ሥራ ላይ የተሰማራ ሲሆን በሂላሪና ጋለን የገንዘብ ድጋፍ አገልግሎት በሚሰጥባቸው ፕሮጄክት አካባቢዎች ለሚግኙ ትምህርት ቤቶች ግብኣት የሚዉል የተማሪዎች መቀመጫ ዴስክ (combined desk) እና ጥቁር ሰሌዳ (Black board ) በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

S/NDescriptionQty
1የተማሪዎች መቀመጫ ዴስክ (combined desk)2000
2ጥቁር ሰሌዳ (Black board)330

ስለሆነም

➢ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉበት እና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ

➢ የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ CPO ለ30 ቀናት የሚቆይ ከሚያቀርቡት ዋጋ ላይ ከቫት ውጭ 2% ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ለብቻ በታሸገ ኢንቨሎፕ ማስያዝ የሚችሉ

➢ ስለጨረታው የሚገልፀውን ሰነድ የማይመ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) እና የታደሰ ንግድ ፈቃዳቸውን ማቅረብ ይኖርባቸዋል

➢ ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነዱን መቀሌ ከተማ ከሚገኘው ዋና መስሪያቤት ጥር 29 2016 እስከ የካቲት 8 2016 ዓ/ም ባለው የስራ ሰዓት የጨረታ ዶክመንቶችን መግዛት ይችላሉ፡፡

➢ የሚወዳደሩበትን ዋጋ የድርጅቱን ማህተም ባለዉ ኢንቨሎፕ አንድ ኮፒ እና አንድ ኦርጂናል በማድረግ እና የጨረታ ማስከበሪያ ዎስትና ለብቻው በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ የካቲት 8 2016 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል

➢ ተጫራቾች ከዚህ ደብዳቤ ጋር የተያያዘውን ዝርዝር ዕቃዎች ዋጋ በመሙላት የካቲት 8 2016 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ሰዓት ላይ ራሳቸው ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው (በሰንዶች ማረጋገጫ የተረጋገጠ ህጋዊ ውክልና የያዙ ወኪሎቻቸው) መቀሌ ከተማ የድርጅቱ ዋና ፅሕፈት ቤት ጨረታው ይከፈታል::

➢ በድርጅት የውክልና ዳብዳቤ እንደማንቀበል በትህትና እንገልጻልን።

➢ ድርጅቱ ለተሻለ ኣማራጭ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ:-ኢማጂን ዋን ደይ ኢንተርናሽናል ኦርጋናይዜሽን ዓዲ ሓዉሲ ገበያ በስተጀርባ የድርጅቱ ጽፈት ቤት መቐለ

የቀጥታ ስልክ ቁጥር - 0900309130/0914141190/0911363401

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo