በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማሕበር የትግራይ ክልል ቅ/ጽ/ቤት ከERCS WASH ፕሮጀክት በሰሜናዊ ምእራበ ዞን ለሚያከናውነው የተለያዩ እንቅስቃሴዎች የሚያገለግሉ የተለያዩ ንብረቶች ( ቁሳቁሶች) በቀረበው ስፔስፊኬሽን መሰረት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈለጋል።

በኢትዩጵያ ቀይሕ መስቀል ማሕበር የትግራይ ቅርንጣ

የግልፅ ጨረታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማሕበር የትግራይ ክልል ቅ/ጽ/ቤት ከERCS WASH ፕሮጀክት በሰሜናዊ ምእራበ ዞን ለሚያከናውነው የተለያዩ እንቅስቃሴዎች የሚያገለግሉ የተለያዩ ንብረቶች ( ቁሳቁሶች) በቀረበው ስፔስፊኬሽን መሰረት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈለጋል። ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጨራቶች። በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። ተጫራቶች፡-

1. የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ

2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማረጋገጫ ማቅረብ የምትችሉ

3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የተመዘገባችሁ

4. በአቅራቢነት የተመዘገባችሁ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ

5. የማይመለስ ብር 50.00 (ሃምሳ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነድ ከቢሮ ቁጥር 10 በስራ ሰዓት ከ17/05/2016 እስከ 1/06/2016 ዓ/ም መውሰድ ትችላላችሁ

6. ተጫራቶች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በትክክል ሞልታችሁ በማሸግ እስከ 1/06/2016 ዓ/ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይቻላል፡፡ በተጨማሪም ለውድድር ለጨረታ ያቀረባቹሁት ዋጋ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ /validity period/ መጠቀስ አለበት፡፡

7. ተጫራቶች አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶች በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው።

8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብር 10% ካቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አይፈቀድም፡፡

9. የጨረታ ሰነድ የሚከፈትበት ቀን 1/06/2016 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ሲሆን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪላቸው ጨረታው በሚከፈትበት ቀንና ሰዓት ቢገኙ ይመረጣል፡፡ ሆኖም ግን ባለመገኘታቸው ጨረታው አይስተጓጎልም፡፡

10. አሸናፊ ተጨራቾች ጨረታው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ የማሰር ግዴታ አለበት ቀናት ውስጥ ቀርቦ ውል

11. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ቀይሕ መስቀል ማሕበር የትግራይ ክልል ቅ/ጽ/ቤት ለተጨማሪ ማብራሪያ፡-

በስልክ ቁጥር -- 0344-408864 መደወል ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo