የትግራይ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽ ቢሮ ከUIDP በጀት ለቢሮው ግልጋሎት የሚውል

የትግራይ ክልላዊ መንግስት ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ

ግልፅ የጨረታ ማስታወቅያ
የጨረታ ቁጥር 5/2016

የትግራይ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽ ቢሮ ከUIDP በጀት ለቢሮው ግልጋሎት የሚውል

ሎት 1. ቶታልስቴሽን

ሎት 2. ፈርኒቸር እቃዎች በግልፅ ጨረታ ኣወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። በዚህ መሰረት መወዳደር የምትፈልጉ፤

1. በዘርፉ 2016 ዓ/ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል፣

2. በዘርፉ 2016 ዓ/ም የታደሰ ኣቅራቢነት ማቅረብ የሚችል፣

3. የተጨማሪ እሴት ታክስ ቫት ተመዝጋቢ የሆነ ማቅረብ የሚችል

4. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ናምበር ማቅረብ የሚችል

5. የመሰከረም 2016 ዲክለር ያደረጉበት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።

6. ተጫራቾች የጨረታው ሰነድ ከ 15/5/2016 እስከ 27/5/2016 ከትግራይ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 59 የማይመለስ ብር 100 /መቶ ብር/ ወደ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000538910318 ገቢ በማድረግ መውሰድ ይችላሉ፡፡

7. ጨረታው በ 27/5/2016 ከቀኑ 4፡00 ሰኣት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በትግራይ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ግዥና ንብረት ኣስተዳደር ዳይሬክቶሬት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 59 የሚከፈት መሆኑን እየገለፅን ተጫራቾች ባለመቅረባቸው የማይከፈት ሰነድ የለም፡፡

8. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ ለቶታልስቴሽን 100,000 /መቶ ሺ/ ብር ለፈርኒቸር 5,000 /አምስት ሺ/ በCPO ፣በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና፤ በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል።

9. ተጫራቾች የመወዳደርያ ሰነድ ዋጋ ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ኢንቨሎፕ ከ 15/5/2016 እስከ 27/5/2016 እስከ 4፡00 ሰዓት ትግራይ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽ ቢሮ ግዢና ንብረት ኣስተዳደር ዳይሬክቶሬት 1 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 59 በማቅረብ ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል

10. ተወዳዳሪዎች የሚያቀርቡት ሰነድ ከስርዝ ድልዝ የፀዳና በእያንዳንዱ ገፅ ማህተምና ፌርማ መኖር ኣለበት።

11. ሰነድ ጨረታ በሙሉም ሆነ በከፊል ማስቀረት ከጨረታ ዉጪ ያደርጋል።

12. ተጫራቾች ሰነድ ላይ የተዘረዘሩትን ዕቃዎች ኣሸናፊ ከሆኑት ውል ከታሰረበት በ 15 ተከታታት ቀናት እቃው ማስገባት የሚችል።

13. ቢሮው የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 034-240-01-29 ወይም 0914728013 መደወል ይችላሉ።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo