የጨረታ ማስታወቅያ ሞሓ የለስላሳ መጠጦች ኢንዳስትሪ ኣ/ማ የመቐለ ፔፕሲ ኮላ ፋብሪካ ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ያገለገሉ ንብረቶች በጨረታ ኣወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

Moha Soft Drinks Industry

 ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ መመርያ ኣክብራችሁ ለመጫረት የምትፈልጉ ተጫራቾች ሁሉ መጫረት የምትችሉ መሆኑ በኣክብሮት እንጋብዛለን ፡፡ የጨረታ መመርያ

1. ተጫራቶች ህጋዊና የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው

2. ተጫራቶች ለጨረታው ማስከበርያ በጥረ ገንዘብ ብር 3000 ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

3. ሁሉም ተጫራቾች ከ 06/05/2016 ዓ/ም እስከ 10/05/2016 ዓ/ም መቐለ ዩኒቨርሲቲ (አሪድ) ፊት ለፊት በፋብሪካው ቅጥር ግቢ በሚገኘው ሞሓ የለስላሳ መጠጦች ኢ/ሪ ኣክስዮን ማህበር መቐለ ፋብሪካ ካፍቴርያ በመምጣት እና የማይመለስ ብር 100 በመክፈል የጨረታ ሰነድን መግዛት ይችላሉ፡፡

4. ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የቀረቡ ቅፆች በትክክል እና ስርዝ ድልዝ በሌለበበት ሁኔታ ሞሙላት ኣለባቸው፡፡ እንዲሁም በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ገፅ እና የሰነዱ ማሸግያ ፖስታ የተጨራቶች ህጋዊ ማህተም ወይም ስም እና ፊርማ መኖር ይኖርበታል፡፡ 

5. የጨረታው ሳጥን 11/05/2016 ዓ/ም ጥዋት ልክ 3:15 ሰዓት የሚታሸግ ሲሆን ከዚሁ ሰዓት በኃላ የጨረታ ሰነድ ይዞ የሚመጣ ተጫራች ተቀባይነት ኣይኖሮውም፡፡

6. ጨረታው ተጨራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወይም ባልተገኙበት 11/05/2016 ዓ/ም ጥዋት ልክ 3፡30 በፋብሪካው ካፍቴርያ ውስጥ ይከፈታል።

7. ተጨራቾች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ በመንተራስ ዋጋ ማቅረብ ኣይችሉም።

8. ተጨራቾች ለጨረታ በመልክ በመልኩ የተዘጋጀውን ዕቃ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ ጨረታው መዝጊያ ቀን ድረስ በፋብሪካው ግቢ ውስጥ መመልከት ይችላሉ። ለጨረታ የቀረበው ዕቃ ድርጅቱ የሚመድበው ሠራተኛ ለተጫራቾች ያሳያል፣ ተገቢውን ማብራርያ ይሰጣል፡፡

9. ተጨራቾች ማሸነፋቸው ከተገለፀበት ግዜ ጀምሮ በሦስት ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ ለድርጅቱ ገቢ በማድረግ ንብረቱ በ10(ኣስር) ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህ ሳይሆን ሲቀር ግን ለያንዳንዱ ቀን በጨረታው ዋጋ ላይ ብር 2% የመጋዘን ኪራይ ይከፍላል፡፡

10. በዚህ ጨረታ የቀረቡ እቃዎች ብዛታቸው ጨምሮ ቢገኝ ኣሸናፊው ለተጨማሪው መጠን ክፍያ ፈፅሞ ሊወስድ ይችላል።

11. ተጨራቾች በሚያቀርቡት ዋጋ ላይ ጠቅላላ ዋጋው የሂሳብ ስሌት ስህተት ቢኖረው በኣቀረቡት የነጠላ ዋጋ መሠረት ተባዝቶ የሚገኘው ጠቅላላ ዋጋ ተቀባይነት ይኖረዋል።

12. በጨረታው ኣሸናፊ ላልሆኑ ተወዳዳሪዎች ያስያዙት የጨረታ ማስከበርያ በጥረ ገንዘብ ብር 500 የጨረታው ኣሸናፊ እንደታወቀ ይመለስላቸዋል። ድርጅቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ በማንኛውም ግዜ ጨረታው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ ፡ በስልክ 0913377007 ደውሎ መረዳት የሚቻል መሆኑ እናስታውቃለን፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo