የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አዲ-ግራት መንገድ ጥገና ዲስትሪክት የተለያዩ የሰራተኞች ጥቅማ ጥቅም (አልባሳት ፣ ጫማ ፣ የመፀዳጃ ወረቀት ፣ የልብስ ሳሙና ፣ የገላ ሳሙና) እንዲሁም ኮምፒውተርና ላፕቶፖች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የኢትዩጰያ መንገዶች ባለሥልጣን

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አዲ-ግራት መንገድ ጥገና ዲስትሪከት የተለያዩ የሰራተኞች ጥቅማ ጥቅም/አልባሳት፣ ጫማ ፣ የመፀዳጃ ወረቀት ፣ የልብስ ሳሙና ፣ የገላ ሳሙና/ እንዲሁም ኮምፒውተርና ላፕቶፖች በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ ብቁ ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡

  1. በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ድርጅቶች በኢትዮጵያ ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በመንግስት ዕቃና አገልግሎት አቅራቢነት በኤጀንሲው ደህረ ገፅ Website/ የተመዘገቡ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  2. በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቶች በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ለመሳተፍ የሚያስችል የዘመኑን ግብር የከፈሉበት ከሚፈልገው ግዥ የተዛደ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እና በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ለመሳተፍ ከሀገር ውስጥ ገቢዎች ቢሮ ግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው ማስረጃ በማቅረብ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት‍‍‍‍‌‍‌‍‌‌‌‍‍‍‌‍ ሜክሲኮ ከሚገኘው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና መ/ቤት /አዲስ አበባ/ በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ከወጣበት ቀን ጀምሮ መግዛት ይችላሉ፡፡
  3. የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው አሸናፊ የሚሆነው በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነድ ውስጥ በተመለከቱት መስፈርቶች መሠረት ሲሆን ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውም አቅራቢ ከፍት ነው፡፡ የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነድ የተዘጋጀው በአማርኛ ቋንቋ ነው፡፡
  4. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ብር 50,000 /ሃምሳ ሺህ ብር/ የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስከበሪያ የባንክ ዋስትና ከጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነዶች ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ውጭ በኢንሹራንስ ወይም በሌላ መልከ የሚቀርብ የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነዳቸው ለዚህ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ አዲስ አበባ ዋና መ/ቤት ግዥ ቡድን ገቢ የሚያደርጉበት የመጨረሻ ቀን ታህሳስ 02/2016 ዓ.ም እስከ ጠዋቱ 4:00 ሰዓት ድረስ ብቻ ነው፡፡
  6. ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸውን በተገኙበት ታህሳስ 02/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት አ/አ ዋና መ/ቤት በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
  7. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የበለጠ መረጃ- ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፡፡

ሞባይል፡- 09-29-72-66-38/09-48-50-93-27 ወይም 09-38-17-64-17

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

የአዲግራት መንገድ ጥገና ዲስትሪክት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo