የኢትዮዽያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የመቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ያሉትን ተሸከርካሪዎች ሰርቪስ ለማድረግና ጥገና የሚያስፈልጋቸውን ለማስጠገን ባለ ጋራዦችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ከአሸናፊ ድርጅት ጋር ለሁለት ዓመት ውል ለማሰር ይፈልጋል፡፡

መቐለ ስታስቲክስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት የምታሟሉ የጋራ ድርጅቶች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እየጋበዝን

1. የ2015 ዓ/ም ግብር የከፈለ ድርጅት

2. የቫት ተመዝጋቢ የሆነና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለው

3. በመንገድ ትራንስፓርት ቢሮ ወይም ፅ/ቤት በኩል ሁለተኛ ደረጃ እና ከዚህ በላይ የብቃት ማረጋገጫ ወይም ደረጃ (Standard) ማስረጃ የተሰጠው መሆኑን የሚያቀርብ

4. የተሟላ ግቢ የቴክኒክ ሙያተኞችና ማሽነሪዎች ያሉት የራሱ ኤሌክትሪካን ቦዲማን ኢንጅን የመፈተሻ ጉድጓድ ያለው

5. ከቅ/ጽ/ቤቱ(መቐለ ስታቲስቲክስ) ጋር ለሁለት ዓመት ውል ለመፈራረም ፈቃደኛ የሆነ

የጨረታ ሰነድ ዝርዝር ከመቐለ ስታቲስክስ ቅ/ፅ/ቤት የግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ክፍል ኮፒ አድርጎ በመውሰድ በሰነዱ ላይ በተቀመጠው የእጅ ዋጋ ሰንጠረዥ የምትወዳደሩበትን ዋጋ በብርና በሳንቲም በግልፅ በመሙላት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 የሥራ ቀናት ለቅ/ፅ/ቤቱ ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር አስተባባሪ ማቅረብ የምትችሉ ሲሆን የቀረቡትን የጨረታ ሰነዶች በፅ/ቤቱ የግዥና የፕሮፎርማ ኮሚቴ ከ15 ቀናት በኃላ ተከፍቶ የሚታይና አሸናፊው ድርጅት የሚለይ ይሆናል፡፡ አሸናፊ ድርጅቱም በአድራሻው ያሸነፈ መሆኑ ከተገለፀለት በኃላ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከቅ/ፅ/ቤቱ ጋር ውል ይፈፅማል፡፡

ስልክ ቁጥር 0344410708

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo