የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጉምሩክ ኮሚሽን የመቀሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የተለያዩ አገልግሎቶች እና ዕቃዎችን ብቃትና ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የኢትዮጸያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጉምሩክ ኮሚሽን የመቀሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን አገልግሎቶች እና ዕቃዎችን ብቃትና ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ በመንግሥት ግዥ አዋጅ እና መመሪያ በተገለጸው ብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ሥነ-ሥርዓት መሠረት የሚገዛቸው አገልግሎቶች እና ዕቃዎች እንዲሁም በእያንዳንዱ የአገልግሎትና ዕቃ የሚፈለግ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና መጠን ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የአገልግሎትና የዕቃ ሎት ቁጥሮች መሠረት በማድረግ ነው፡፡

  1. ሎት 01- ለመቆጣጠሪያ ጣቢያ የሙሉ ቀን የመኪና ኪራይ አገልግሎት የሚያስፈልገው የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 20,000.00
  2. ሎት 02 - ለተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች እና የመኪና ጎማዎች የሚያስፈልገው የጨረታ ማስከበሪያ መጠንብር 35,000.00
  3. ሎት 03 - ለፅሕፈት መሳሪያዎች የሚያስፈልገው የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 30,000.00
  4. ሎት 04 - ለጽዳት ዕቃዎች የሚያስፈልገው የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 30,000.00
  5.  ሎት 05 - ለኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች የሚያስፈልገው የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 60,000.00
  6. ሎት 06 - ለፈርኒቸር ዕቃዎች የሚያስፈልገው የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 20,000.00
  7. ሎት 07 - ለመጋረጃ እና መስቀያው የሚያስፈልገው የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 30,000.00
  8. ሎት 08 - ለደንብ ልብስ የሚያስፈልገው የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 48,000.00
  9. ሎት 09 - ለእሽግ ውሃ አቅርቦት የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 60,000.00
  10. ሎት 10- ለሕትመት አገልግሎቶች የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 10,000.00
  11. ሎት 11- ለጥገና አገልግሎቶች / የIT የፈርኒቸሮች ሌሎች/ የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 10,000.00
  12. ሎት 12 - ለውሃ ቦቴ ኪራይ አገልግሎት የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 10,000.00
  13. ሎት 13 - ለደረቅ ጭነት አገልግሎት የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 10,000.00

የግዥ ጨረታ የሚከናወነው ብቁ ከሆነ ተጫራች እና ከአገልግሎቱ እና ከዕቃዎች ጋር አግባብነት ያላቸው የ2016 በጀት ዓመት የታደሰ ህጋዊ የንግድ ስራ ፍቃድ ያለው ፣ የዘመኑ ግብር መክፈላቸውን የሚገልጽ ታክስ ክሊራንስ እና በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም ዲክለር ያደረጉበት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል ፣ በአቅራቢነት የተመዘገበ መሆኑን ማስረጃ የሚያቀርብ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ እና ተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል ሆን አለበት፡፡

ተጫራቾች በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ የማይመለስ ብር 200.00 ( ሁለት መቶ ብር) ከፍለው የጨረታ ሰነዱን ከዚህ በታች በተገለጸው አድራሻ በአካል በመገኘት መውሰድ ይችላሉ፡፡

ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን ከዚህ በታች በተራ ቁጥር 7 በተገለጸው አድራሻ የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥቅምት 06 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 4፡00 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡ ጨረታው በተመሳሳይ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጥቅምት 06 ቀን ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 4፡30 ላይ ይከፈታል፡፡

ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ከላይ በተራ ቁጥር 2 በተገለጸው ለእያንዳንዱ የሎት ምድብ የተቀመጠውን የገንዘብ መጠን በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡

የጨረታው ሰነድ የሚገባበት አድራሻ ትራንስ ኢትዮጵያ አጠገብ የሚገኘው የውሃንስ ግደይ ሕንጻ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ፅሕፈት ቤት 2ኛ ፎቅ ሃብት አስተዳዳር ሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 11 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ይሆናል።

ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በከፊልም ሆነ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብት አለው።

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0914 83 04 69/0919 06 83 85 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo