አፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ የተለያዩ የትምህርት መርጃ መሣርያዎች፣ ህትመት እና ቪዝቨሊቲ ቦርድ በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ አቅራቢዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የኣፋር ትምህርት ቢሮ

  • ጨረታዉ  በጋዜጣ የወጣበት ቀን ፡  13/9/2013      
    ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን ፡ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ
    ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን ፡ በ11ኛዉ የስራ ቀን በ 3:00  ሰዓት ይከፈታል

  • ተለያዩ የትምህርት መርጃ መሣርያዎች፣
  • ህትመት እና
  • ቪዝቨሊቲ ቦርድ በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ አቅራቢዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር(TNT) ያለው፡፡
  2. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የትምህርት መርጃ መሣርያዎች፣ ህትመት እና ቪዝቨሊቲ ቦርድ አቅርቦት አስመጭ መሆናቸውን ከአሁን በፊት አግባብነት ካለው የመንግስት መ/ቤት ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እንደሚሰጡ ማስረጃ  ማቅረብ የሚችል፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር  አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ ሠመራ ትም/ቢሮ ቁጥር 5  የጨረታውን ሰነድ በመግዛት የሚወዳደሩበትን ሀሳብ እና ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነዶች በመለየት በ2 ኮፒ ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጣን ማስገበት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 2% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረት የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ትምህርት ቢሮ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ዋና የስራ ሂደት ክፍል ቢሮ ቁጥር 5 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል ::
  8.  ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በትምህርት ቢሮ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 6 በ11ኛው የስራ ቀን በ3፡00 ሠዓት ይከፈታል፡፡
  9.  ለአሸናፊው ተጫራች የሚከፈል ቅድሚያ ክፍያ አይኖርም፣ በመሆኑም አቅርቦቱን በተገቢ ሁኔታ በስፔስፊኬሽን መሠረት አቅርቦቱን ማቅረቡ  ሲረጋገጥ 100% ክፍያ ወዲያውኑ ይፈፀምለታል፡፡
  10. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ  የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ተጫራች ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ  ከፈለጉ ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የስራ ሂደት ክፍል ቢ ቁጥር 5 በስልክ ቁጥር 033-666-01-26/033666-01-23 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

አፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ

ሠመራ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo