መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለምርት አገልግሎት የሚጠየቀው 180,000 ሜትሪክቶን የሀገር ውስጥ የድንጋይ ከሰል አቅራቢዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

መሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ
  1. የጨረታ ቁጥር 39
    በጨረታው የሚሳተፉ ድርጅቶች በዘርፉ የተሰማሩ መሆናቸው የሚገልፅ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸው፣ የመዓቱን ፈቃድ፣ የመዕድን ፈቃድና የመሬት ይዞታ ሰርተፊኬት የሚገልፅ ማስረጃ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
  2.  ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ ዋስትና ብር 500,000 (አምስት መቶ  ብር) በመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማ ስም የተዘጋጀ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (CPO) ወይም ባንክ ጋራንቲ ከቴክኒካል ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከላይ በተራ ቁጥር 2 ከተጠቀሱት ማስረጃዎች ጋር በማያያዝ የድርጅታቸውን አርማና ማህተም ያለው ደብዳቤ በመፃፍ ለጨረታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  4. ተጫራቾች ከዚህ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ጋር አብሮ ከተገለፀው ዝርዝር መግለጫ መሰረት ያቀርቡትን የሃገር ውስጥ ድንጋይ ከሰል በጨረታው ቀን ወይ ከዛ በፊት በራሳቸው ወጪ ለምርመራ ናሙና (ሳምፕል) ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። (ናሙናው የሚቀርበው መቀሌ በሚገኘው ዋና ፋብሪካ ይሆናል)
  5. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረብያቸውና በተራ ቁጥር 2 እና 3 ላይ የተጠቀሱት ሰነዶችና በተራ ቁጥር 5 የተጠቀሰውን ናሙና (ሳምፕል) እስከ ጥቅምት 24/ 2013 ከሰዓት በኃላ 800 ሰዓት ድረስ በታሸገ ኢንቨሎፕ የጨረታ ሰነዳቸው መቀሌ በሚገኘው የፋብሪካው ዋና መስራ ቤት 3ኛ ፎቅ ቁጥር 15 ስለሚገኝ የግዥና አቅርቦት ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  6.  ጨረታው በእለቱ ጥቅምት 24/2013 ከሰዓት በኃላ 830 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 100 (አንድ መቶ ብር )በመክፈል መግዛት  የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
  8. ፋብሪካው ጨረታው በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
  9.  ለተጨማሪ ማብራርያ በስልክ ቁጥር +251912502596/ +251914729516/ 0115581735 ወይም procurementmessebocement2020@gmail.com  መጠቀም ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo