በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን ዕዝ ጠ/መምሪያ ለ2013 በጀት ዓመት እገልግሎት የተለያየ የጽሕፈት መሳሪያ፣ የተለያዩ የፅዳት ዕቃዎች፣ የጀኔረተር እና የማሽነሪ መለዋወጫ ዕቃዎች፣ በግልጽ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

በሀገር መከላከያ ሚኒስትር የሰ/ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ

ቁጥር 02/2013 

  • ሎት 1 የተለያየ የጽሕፈት መሳሪያ፣ 
  • ሎት 2 የተለያዩ የፅዳት ዕቃዎች፣ 
  • ሎት 3, የጀኔረተር እና የማሽነሪ መለዋወጫ ዕቃዎች፣                                                                
  • በዚህም መሠረት ከሎት1 እስከ ሎት 2 ለተጠቀሱት በዘርፉ የተሰማሩ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ ሠርተፊኬት፣ የቫት ሠርተፊኬት እና የኣቅራቢነት ምዝገባ ሠርተፊኬት ያላቸውን ይጋብዛል፡፡ 

    ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መመሪያ እና ዝርዝር ሰነድ የያዘ ለሎት 1 እና ለሎት 2 ለእያንዳንዳቸው 100,00/ አንድ መቶ ብር/ እንዲሁም ለሎት3 50.00/ ሃምሳ ብር በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት መቐለ ኩሓ መንገድ እግሪ ወንበር አካባቢ ከሚገኘው የሰ/ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ግዥ ቡድን ቢሮ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመግዛት በቢሮው ወደ ተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ጨረታው መስከረም 4 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 

    • መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 
    • ለተጨማሪ ማብራሪያ ስ.ቁ 0344-41-07-50 

    በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የሰሜን ዕዝ 

    ጠ/መምሪያ 


ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo