የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ በ2013 ዓም ለቢሮው ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውሉ ጎማዎችና የተለያዩ የትምህርት መረጃ መሳሪያ Learning material በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ አቅራቢዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የኣፋር ትምህርት ቢሮ
  • ሎት 1ጎማ
  • ሎት 2 የትምህርት መርጃ መሳሪያ Learning material  (ሞንቶሶሪ) 
  1.  በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፣ 
  2. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  3. በሚሳተፉበት አቅርቦት ጨረታ ክፍል አግባብ ካለው የመንግስት መ/ ቤት ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀየአገልግሎት አቅርቦትእንደሚሰጡ የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራቁጥር 1-5 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣባት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ቅዳሜና እሁድን)ጨምሮሠመራትም/ቢሮቁጥር 5 የጨረታውን ሰነድ በመግዛት የሚወዳደሩበትን ሀሰብ እና ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነዶችን በመለየት በ2 ኮፒ ለዚሁ በተዘጋጀሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 2% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ( ሲፒ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፣
  7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጂዎች ማለትም ዋና እና ቅጂ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ትምህርት ቢሮ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ክፍል ቢሮቁጥር 5 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል። 
  8. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በትምህርት ቢሮ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 6 በ16ኛዉ ቀን በ3፡00 ሠዓት ይከፈታል፡፡ 
  9. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  10. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ተጫራች ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 5 በስልክ ቁጥር 033666 01-25/0920 0091 09 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡ 

የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ (ሰመራ) 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo