በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ በዚህ በ 2013 በጀት ዓመት የተለያዩ የችግኝ (ቡቃያ) ፣ የውሀ ቦቲ መኪና ኪራይ ፣ የሽንኩርት ዘር ፣ የቲማቲም ዘር ፣ የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት (የመኪና ኪራይ) የተለያዩ የመኪና መለዋወጫ ዕቃ እና የመኪና ጎማና ከነከለማዳሪያው በአገር ውስጥ ገበያ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

አፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የእንስሳት፤እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ
  • የችግኝ (ቡቃያ)፣
  • የውሀ ቦቲ መኪና ኪራይ፣
  • የሽንኩርት ዘር፣
  • የቲማቲም ዘር፣
  • የደረቅ ጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት (የመኪና ኪራይ)
  • የተለያዩ የመኪና መለዋወጫ ዕቃ እና
  • የመኪና ጎማና ከነከለማዳሪያው በሀገር ውስጥ ገበያ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
  • 1.ተጫራቾች ግዴታ ማሟላት ያለባቸው የቅድሚያ መወዳደሪያ መስፈርት ማለትም፡- 
    • 1.1. በዘርፉ የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ 
    • 1.2. የንግድ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ያለው 
    • 1.3. ንግድ ፈቃድ ምዝገባ ሰርተፍኬት 
    • 1.4. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ 
    • 1.5. ሲፒኦ 
    • 1.6 የጨረታ ሰነድ ግዥ የፈፀመ እና
    • 1.7. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያለው ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚጭሉ 

    2. በጨረታው ለመሳተፍ አየምትፈልጉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታው ሰነድ ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ በግዥ /ፋይ/ንበ/አስ/ደጋፊ የስራ ሂደት ክፍል ብር 100.00/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ ይጭላሉ፡፡

     3.ተጫራቾች በእያንዳንዱ በሚያቀርቡት የጨረታ ሰነዶች ላይ ተጫራቾች ወይም የህጋዊ ወኪል ፊርማና ማህተም ማኖር ይኖርባቸዋል፡፡ 

    4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና /bid bond/ ለውድድር የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 1% በሲ.ፒ.አ (C PO) የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ተወዳዳሪዎቸ በወድድሩ ከተሸነፈ ለዋስትና ያስያዙት የጨረታ ማስከበርያ ዋስትናና እንዲሁም ናሙና የጨረታው ውጤት ታውቆ ውል ከተፈራረሙ በኋላ ወዲያውኑ ማስከበርያ ይመለስላቸዋል፡፡ 

    5. ጨረታው ከተከፈተ በኃላ ማንኛውም ተጫራች የሚያቀርቡትን የውድድር ጥያቄ መ/ቤቱ አይቀበልም 

    6.ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታተይ 15 ቀናት የሚቆይ ሆኖ በ15ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ የሚዘጋ ሲሆን በእለቱ 4፡30 ሰዓት በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በኣፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የእንሳሳት እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ  ወኪሎቻው በተገኘበት ይከፈታል፡፡ 

    7. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በመሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

    8, ለተጨማሪ መረጃ በቢሮው ስልክ ቁጥር 033-366-60 22 ደውለው ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡ 

    በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት 

    የእንስሳት እርሻና ተፈጥሮ ሀብት 

    ልማት ቢሮ 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo