በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮምሽን መቐለ ቅ/ጽ/ቤት የሠራተኞች ሰርቪስና የሙሉ ቀን ኪራይ አገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል

የኢትዮጸያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን
  1. ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ
  2. የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ ወይም በትግራይ ክልል እቅድና ፋይናንስ የተዘጋጀው የአቅራቢነት ፈቃድ ማቅረብ፡፡
  3. ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለሥልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ፡፡
  4. ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት፡፡
  5. የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 በባንክ በተመሠከረለትቼክ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ ትራንስ ኢትዮጵያ አጠገብ ዮሐንስ ግደይ ህንፃ ከሚገኘው የቅ/ጽ/ቤቱ ሃብት አስተዳደር ስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 11 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ሰኔ 26/2012 ዓም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል:: ጨረታውም በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት በመስሪያ ቤቱ ሁለተኛፎቅ ሃብት አስተዳደር የስራሂደት ቢሮ ቁጥር 11 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  8. የጨረታው አሸናፊ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና 10% (አስር በመቶ) CPO በማስያዝ ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማል::
  9. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
  10. ተጫራቾች ዋጋው ከነቫቱ መሙላት ይጠበቅባቸዋል።
  11. የሙሉ ቀን ኪራይ አገልግሎት ላይ የሚቀርቡ መኪኖች የስሪት ዘመን ከ2011-2019 ባለው ውስጥ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡

ስልክ ቁጥር- 034 24071 62/0919 06 83 85/0914 83 04 69 ፋክስ- 034 440 73 09

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮምሽን የመቐለ ቅ/ፅ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo