አፍሪካ ኢንሹራንስ ኩባንያ በግጭትና በመገልበጥ አደጋ ጉዳት ደርሶባቸው ለደንበኞች የካሣ ክፍያ ፈፅሞ የተረከባቸውን የተለያዩ አይነት ከባድና ቀላል ተሽከርካሪዎችን እና የተለወጡ አሮጌ የተሽከርካሪ ዕቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

Africa Insurance Company S.C
  1. የመኪኖቹን/ንብረቶቹን ሁኔታ ማየት የሚፈልጉ ተጫራቾች እስከ ረቡዕ ሰኔ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ተሽከርካሪዎቹን በስራ ሰዓት ማየት የሚችሉ ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ የሚገኙበት አድራሻ፡1.1 በአፍሪካ ኢንሹራንስ ጉዳት የደረሰባቸው ተሽከርካሪዎች ማቆሚያ ቦታ ቃሲቲ ኖክ ማደያ በሚድሮክ ተርሚናል ወደ ውስጥ 1.5 ኪ.ሜ ገባ ብሱ የተጎዱ መኪኖች ማቆያ ቅጥር ግቢ፣ 1.2 መቀሌቅርንጫፍ 
  2. ስለአሻሻጡ የተዘጋጀውንና የተሽከርካሪዎቹን/ንብረት ዝርዝር የያዘውን ፎርም ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ቦሌ ሩዋንዳ አፍሪካ ኢንሹራንስ ኩባንያ ሕንፃ በሚገኘው በኩባንያው ዋናው መ/ ቤት ወይም ከላይ በተራ ቁጥር 1 ላይ በተገለፀው ስፍራ በመገኘት እስከ ረቡዕ ሰኔ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ የማይመለስ 50 ብር በመክፈል ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡ 
  3. ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጉትን የእያንዳንዱን ተሽከርካሪ/ንብረት ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ ረቡዕ ሰኔ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡ 00 ሰዓት ድረስ ቦሌ ሩዋንዳ በሚገኘው በኩባንያው ዋና መ/ቤት ካሣ መምሪያ ለዚሁ በተዘጋጀ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  4. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ተሽከርካሪ/ንብረት የመነሻ ዋጋ 20% (ሃያ በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ(CPO) ማስያዝ የሚኖርባቸው ሲሆን ይህን መስፈርት የማያሟላ ተጫራች ወዲያውኑ ከጨረታው ይሰረዛል፡፡ ተጫራቹ በጨረታው ከተሸነፈ በማስያዣ ያስያዘው ገንዘብ ወዲያውኑ ተመላሽ ይሆንለታል፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ሲሞሉ የሚጫረቱበት ዋጋ ከቫት በፊት መሆን አለበት፡፡ 
  6. ጨረታው ሐሙስ ሰኔ 11 ቀን 2012 ዓ.ም. ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ቦሌ ሩዋንዳ በአፍሪካ ኢንሹራንስ ኩባንያ ዋናው መ/ቤት ውስጥ የሚከፈት ሲሆን ኮቪድ ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል መንግስት ያወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 3/2012 ተግባራዊ ለማድረግ ሲባል ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባልተገኙበት ይከፈታል፡፡ 
  7. ተጫራቾች በጨረታ ያሸነፉትን ተሽከርካሪ/ንብረት ሙሉ ክፍያ 15 % VAT ጨምሮ በ 7 የሥራ ቀናት ውስጥ በመክፈል ማንሳት ይኖርባቸዋል፡፡ በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ ካላነሱ ለአስር ቀናት በየቀኑ 100.00 (መቶ ብር) የማቆሚያ ቦታ ኪራይ የምናስከፍል ሲሆን 10 ቀናት ውስጥ ካላነሱ ግን ያስያዙት ገንዘብ በቅጣት መልክ ለኩባንያው ገቢ ሆኖ አሸናፊነታቸው ይሰረዛል፡፡ 
  8. ለጨረታ በቀረቡት ተሽከርካሪዎችና ንብረቶች ላይ የሚፈለጉ የስም ማዛወሪያ፣ ግብርና ልዩ ልዩ ወጪዎች ቢኖሩ በጨረታው ኣሸናፊ የሚከፈሉ ይሆናሉ፡፡ 
  9. መስሪያ ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው:: 
  10. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0114717340/0116610491 

እንዲሁም ለመቀሌ ተጫራቾች በስልክ ቁጥር፡- 0344-40-19-32 

በመደወል ወይንም በኩባንያው ዋና መ/ቤት በግንባር ቀርቦ መጠየቅ ይቻላል፡፡ 

ማሳሰቢያ፡- ተጫራቾች የሚጫረቱበት ዋጋ ከቫት በፊት መሆን እንዳለበት መሆኑን እንገልፃለን፡፡ 

አፍሪካ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo