በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት ፣ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ በ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት ለማከናወን ካቀዳቸው ግዥዎች ውስጥ የእንስሳት መድሀኒቶች ግዥ በአገር ውስጥ ገበያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

አፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የእንስሳት፤እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ
  1. ተጫራቾች ግዴታ ማሟላት ያለባቸው የቅድሚያ መወዳደሪያ መስፈርቶች ማለትም፡
    • 1.1በዘርፉ የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያለው
    • 1.2.የእንስሳት መድሀኒት ንግድ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ያለው
    • 1.3. የንግድ ፍቃድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ያለው
    • 1.4. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ
    • 1.5. የግብር ክፍያ መለያ ቁጥር /TIN No/ያለው
    • 1.6. ሲፒ ኦማስያዝ አለበት እና
    • 1.7.የጨረታ ሰነድ ግዥ የፈጸመ
  2. በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታውን ሰነድ ከአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ በግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር ብቻበመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች በእያንዳንዱ በሚያቀርቡት የጨረታ ሰነዶች ላይ ተጫራቾች ወይም የህጋዊ ወኪል ፊርማና ማህተም ማኖር ይኖርባቸዋል፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /Bid Bond/ ለውድድር የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 1% በሲፒ.(CPO) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል። የጨረታው ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ከተሸነፈ ለዋስትና ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትናና እንዲሁም ናሙና የጨረታው ውጤት ታውቆ ውል ከተፈራረሙ በኋላ ወዲያውኑ ማስከበሪያ  ይመለስላቸዋል፡፡
  5. ጨረታ ው ከተከፈተ በኋላ ማንኛውም ተጫራች የሚያቀርቡት የውድድር ጥያቄ መ/ቤቱ አይቀበልም፡፡
  6. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 10 ቀናት የሚቆይ ሲሆን በ10ኛው የስራ ቀን 400 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ የሚዘጋ  ሲሆን  በዕለቱ 430 ሰዓት በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት እርሻና ተፈጥሮ  ሃብት ልማት ቢሮ አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  7. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  8. ለተጨማሪ መረጃ በቢሮግዥና ፋይናንስ ንብ/አስ/ ዳይሬክቶሬት ክፍል በቢሮ ቁጥር 08 በአካል በመገኘት ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo