በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት - መቐለ በ2012 በጀት ዓመት ከዋና ግቢ.(ከነባሩ ላብራቶሪ) ወደ አዲሱ ኲሓ ግቢ የተለያዩ የላብራቶሪ ዕቃዎች የማጓጓዝና የኢንስታሌሽን አገልግሎት ስራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

መቐለ ዩንቨርስቲ
  1.  በኤሌክትሮ ሜካኒካል ደረጃ 1 ፈቃድ ያለውና ፍቃዱም በዘመኑ የታደሰ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡ 
  2. የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርቲፊኬት ማቅረብ የሚችል ወይም በግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዌብሳይት የተመዘገ ፡፡
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) የተመዘገበና የምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል፡፡ 
  4. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል፡፡ 
  5. በራሱ ትራንስፖርት ማጓጓዝ የሚችል፡፡ 
  6. ለጨረታ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ) ብር 50,000.00 በባንክ የተመሰከረለት ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ የሚችል፡፡ 
  7. በራሱ ባለሙያ ከነባሩ ላብራቶሪ በመንቀል ወደ አዲሱ ላብራቶሪ ወሰዶ የኢስታሌሽን ስራ መስራት የሚችል፡፡
  8. ለዚህ ሰራ የሚሆን ብቁ ባለሙያዎች ማሽነሪዎች ማጓጓዣና የሰው ሃይል ያለውና አስፈላጊ ሰነድና ፕሮፋይላቸው ማቅረብ የሚችልና።
  9. ማንኛውምተጫራቾች ለዚህ የተዘጋጀ የጨረታ ሰነድ በመውሰድ ነባሩና አዲሱ ላብራቶሪዎች በአካል በማየት ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ዶክመንት ማቅረብ አለባቸው።
  10. ማንኛውም ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ለዚህ ጨረታ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት - መቐለ ዋና ጊቢ ቢሮ ቁጥር 219 መውሰድ ይችላሉ፡፡ 
  11. ተጫራቾች ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 22ኛው ቀን 3፡30 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ጨረታ ተብሎ የተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ። 
  12. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀንና ወር ጀምሮ በ22ኛው ቀን ጠዋት 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ 4:00 ሰዓት ተጫራቾች ህይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልፅ ይከፈታል፡፡ በ 22ኛው ቀን በዓል ከሆነ ደግሞ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡ 
  13. ኢንስቲትዩት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

 ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡-0344412801/ 0344419039 ደውሎ ማነጋገር የሚቻል በመሆኑ በማሳሰብ ጭምር ነው :: 

የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo