በኣፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ማዕድን ሀብት ልማት ጽ/ቤት በበሪህሌ ወረዳ ዓሳ ኣል ሀይቅ በ2012 በጀት ዓመት የጨው መሬት ዝግጅት ሥራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል

አፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ማዕድን ሀብት ልማት ጽ/ቤት
  1. ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ቀን : 24/9/2012
    ጨረታዉ የመዚጋበት ቀን : ሃያ ኣንድ ተከታታይ ቀናት ቀጥሎ ቀን ከጠዋቱ በ3:00 ሰዓት
    ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን : ሃያ ኣንድ ተከታታይ ቀናት ቀጥሎ ቀን ከጠዋቱ በ4:00 ሰዓት
    ዘርፉ የተሰማሩበት በ2012 በጀት ዓመት የታደሰ የንግድ ፍቃድ ፣ የምዝገባ የምስክር ወረቀት TIN ቫት፣ ከክልሉ ኮንስትራክሽን ቢሮ የተሰጠ የብቃት ማረጋገጫ ደረጃ -5 ያላቸው ከሚመለከታቸው ክፍል የተሰጠ ታክስ ክሊራንስ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ የሚችሉ።
  2. ተጫራቾች የስደስት ወር ታክስ ከሊራንስ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ የሚችሉ።
  3. ተጫራቾች ከአሠሪ መ/ቤት የተሰጠ የመልካም ሥራ አፈጻጸም ላለፉት አምስት የበጀት ዓመት ጀምሮ ቢያንስ ሁለት የሥራ አፈጻጸም ማቅረብ የሚችሉ ሆነው የመልካም ሥራ አፈፃፀም የመጨረሻ ዙር ክፍያ የተፈጸመበትና ጊዜያዊ ርክክብ ቬርቫልና የሥራ ውል ከጨረታ ሠነድ ጋር ማቅረብ የሚችሉ።
  4. ተጫራቾች ዝርዝር የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21/ሃያ አንድ ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ለዶክመንት የማይመለስ ብር 300.00 ሦስት መቶ  ብር/ ብቻ በመከፈል በአፋር ማዕድን ሀብት ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 የንግድ ፍቃዳቸውን ዋናውን እና የማይመለስ ኣንድ ኮፒ በመያዝ መግዛት ይችላሉ።
  5. ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋው ከ2% ያላነሰ በ CPOማስያዝ ይኖርበታል።
  6. ማንኛውም ተጫራች የዋጋ ማቅረቢያ ቅጹ የሚጠይቀውን በሙሉ አሟልቶ ማቅረብ ይጠበቅበታል።
  7. ተጫራቾች/Financial/ የዋጋ ማቅረቢያውን ሠነድ እና ቴክኒካል ሠነድ እና ኦርጂናል በአንድ ላይ በማድረግ እና 2 የኦርጂናሉን ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ሙሉ አድራሻውን በመጥቀስ ለዚህ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ መክተት ይኖርባቸዋል።
  8. የጨረታ ሳጥን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ከ21ሃያ አንድ ተከታታይ ቀናት ቀጥሎ በሚውለው በሥራ ቀን ከጠዋቱ በ3:00 ሰዓት ታሽጎ በ4:30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአፋር ማዕድን ሀብት ልማት ጽ/ ቤት ቢሮ ቁጥር 04 ይከፈታል።
  9. ተጫራቾች በክልሉ ሲሠሩ ምንም ዓይነት ማስጠንቀቂያ ያልተሰጣቸው መሆን አለባቸው፡፡
  10. ተጫራቾች በጨረታ መክፈቻ ንባብና በሂሳብ ማስተካከያ ልዩነቱ 2% በላይና በታች መሆን የለበትም ::
  11. ጽ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
  12. የተሞላው ዋጋ መግለጫ ካልተሰጠበት ከነቫት ተደርጎ ይወሰዳል።

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 0911885583

በአፋር ማዕድን ሀብት ልማት ጽ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo