በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሸን በመቀሌ ቅ/ጽ/ቤት የሁመራ ጉም/መቅጣቢያ በሕገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ሊገቡና ሊወጡ ሲሉ የተያዙ አልባሳት፣ ጫማዎች፣ ኤሌከትሮኒክስ የወርቅ ማፈላለጊያ ማሽን፣ ላፕቶፕ የተለያዩ ሞባይሎች ፣ የቀይ ሸንኩርት ዘር፣ ኮስሞቲክስ ነክ ዕቃዎች፣ ፀረ-ነፍሳት፣ የተለያዩ የቤት መገልገያዎች፣ ብረታ ብረት ነክ ዕቃዎች፣ ጣውላ ነከ ዕቃዎች እና ማሽነሪዎች፣ ጀኔሬተር የውሃ ፓምፕ እና ስሊንደር/ ባሉበት ሁኔታ በሐራጅ እና ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

የኢትዮጸያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን
  • አልባሳት፣
  • ጫማዎች፣
  • ኤሌከትሮኒክስ
  • የወርቅ ማፈላለጊያ ማሽን ፣
  • ላፕቶፕ የተለያዩ ሞባይሎች
  • የቀይ ሸንኩርት ዘር፣
  • ኮስሞቲክስ ነክ ዕቃዎች ፣
  • ፀረ-ነፍሳት ፣
  • የተለያዩ የቤት መገልገያዎች፣
  • ብረታ ብረት ነክ ዕቃዎች፣
  • ጣውላ ነከ ዕቃዎች እና ማሽነሪዎች፣
  • ጀኔሬተር የውሃ ፓምፕ እና ስሊንደር/ ባሉበት ሁኔታ በሐራጅ እና ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
  1. 1. በጨረታ በቀረቡት ዕቃዎች ላይ ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች በጨረታ ከሚሸጠው ዕቃ ጋር ተዛማጅነት ያለው የ2012 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፍቃድ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሠርተፍኬት የዘመኑን ግብር የከፈለ ስለመሆኑ ክሊራንስ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ እንቅስቃሴያቸውን ያሳወቁበት በቅርብ ጊዜ የተሰጣቸው የምስክር ወረ እና የንግድ መለያ ቁጥሩን ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር አያይዞ በኤንቨሎፕ በማሸግ ለግልጽ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ያለበት ሲሆን ለሐራጅ ጨረታው ደግሞ በጨረታው ዕለት ይዞ መምጣት ይኖርበታል፡፡ ይሁን እንጂ ለየቤት መገልገያ ዕቃዎች እና የወርቅ ማፈላለጊያ ማሽን የማንኛውም ዘርፍ ንግድ ፈቃድ ያለው ቫት ተመዝጋቢ የሆነ መወዳደር ይችላል፡፡
  2. 2. ተጫራቾት የግልጽ ጨረታውን ሰነድ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ 2፡00-6፡00 ሰዓት ከሰዓት በኋላ ከ9፡00-12፡00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ጠዋት ከ2፡00-6፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል በመቅረጫ ጣቢያው በመሄድ ይህ ጨረታ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ መዝጊያው ቀን ድረስ የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
  3. 3. በግልጽ ጨረታ ለመሳተፍ ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ /5%/ እንዲሁም ለሐራጅ ጨረታ በቀረቡት ዕቃዎች ላይ ለመጫረት ለአልባሳት ብር 25,000 /ሃያ አምስት ሺህ/ ለጫማ ነክ ብር 2,000.00/ ሁለት ሺህ ብር/ ለኮስሞቲክስ ነከ ብር 1,000/ አንድ ሺህ ብር/፣ ለኤሌክትሮኒክስ ብር 500.00/አምስት መቶ ብር ለልዩ ልዩ መገልገያዎች ብር 15,000.00/ አሥራ አምስት ሺህ ብር ለኮንስትራክሽን ማቴሪያል/ ካርታመ ብር 10,000.00/ አሥር ሺህ ብር/ ለኤሌክትሮኒክስ ለወርቅ ማፈላለጊያ ማሽን ብር 100,000.00 ( አንድ መቶ ሺህ ብር) ለሕንፃ መሳሪያዎች ብረታ ብረት እና የእንጨት ነክ ዕቃዎች/ ብር 50,000/ ሃምሳ ሺህ ብር ለማሽነሪ ነክ ዕቃዎች ጀኔሬተር የውሃ ፓምፕ እና ሲሊንደር ጋዝ/ ብር 5,000.00/ አምስት ሺህ ብር/ ለቅባት ነክ ብር 1,500,00/ አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር/ብቻ ለጨረታ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም CPO በሁመራ ጉምሩክ መቅረጫ ጣቢያ ስም በባንክ አሠርተው ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  4. 4. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀን /ስኬጁል/መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡

ተ.ቁ

የመቅ/ጣቢያው ስም

የጨረታው ዓይነት

የንብረት መመልከቻ ቀን

የጨረታው መዝጊያ እና የመክፈቻ ቀንና ሰዓት

1

ሁመራ

ሐራጅ

ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሰባተኛው ቀን

ጨረታው በአዲስ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 8ኛ እና 9ኛ ቀን ከ3፡30 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል፡፡

ግልፅ

በአዲስ ዘመን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሰባተኛው ቀን

ጨረታው በአዲስ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10ኛ ቀን ጠዋት 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 4፡00 ይከፈታል፡፡

  1. 5. የጨረታው መክፈቻ ቦታ፣ በሁመራጉምሩክ መቅረጫ ጣቢያ የሚካሄድ ሲሆን፣ ጨረታው ተጫራቾች ሕጋዊ ወኪሎቻቸው/ባሉበት ወይም በታዛቢዎች ፊት ይካሄዳል፡፡
  2. 6. ለጨረታው አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት (CPO) ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ደግሞ የጨረታው ውጤት ከተገለጸ በ3 ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
  3. 7. አሸናፊ ተጫራቾች ማሸነፋቸውን በደብዳቤ ከተገለጸላቸው ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ ገንዘብ ገቢ ማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡ከላይ በተ/ቁ 7 በተገለጸው ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረገ ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት
  4. 8. ለመ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሚ ለሽያጭ ይቀርባል፡፡
  5. 9. የጨረታው አሸናፊ ከጉምሩክ ንብረቱን ከተረከበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 3 ተከታታይ ቀናት ወደ ንግድ መደብር መሸጫ ቦታው/ ንብረቱን መውሰድ አለበት፡፡
  6. 10. ኮሚሽኑ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  • ለተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥሮች፡- ሁመራ 034-248-5433/034-248-50-65

የሁ/ጉ/መቅ/ጣቢያ ጽ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo