በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅ/ጽ/ቤት የፅሕፈት ዕቃዎች ፣ የፅዳት ዕቃዎች ፣ የመኪና ጎማ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል

የኢትዮጸያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን
  • ሎት አንድ የፅሕፈት ዕቃዎች፣
  • ሎት ሁለት የፅዳት ዕቃዎች፣
  • ሎት ሶሰት የመኪና ጎማ 
  1. ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ። 
  2. የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ወይም በትግራይ ክልል እቅድና ፋይናንስ የተዘጋጀው የአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ 
  3. ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለሥልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ። 
  4. ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስከር ወረቀት። 
  5. የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ ብር 5000.00፣ ለሎት ሁለት ብር 3,000.00 ለሎት ሦስት ብር 10,000. እያንዳንዳቸው በባንክ በተመሠከረለት ቼከ (CPO) ወይም ሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ። 
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመከፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መከፈቻ ቀን ድረስ ትራንስ ኢትዮጵያ አጠገብ ዮሐንስ ግደይ ሕንፃ ከሚገኘው የቅ ጽ/ቤቱ ሀብት አስተዳደር ሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 1 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ። 
  7. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ግንቦት 24/2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል:: ጨረታውም በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት በመስሪያ ቤቱ ሁለተኛ ፎቅ ሀብት አስተዳደር የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 11 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 
  8. የጨረታው አሸናፊ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና 10% (አስር በመቶ) CP0 በማስያዝ ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማል:: 
  9. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  10. ተጫራቾች ዋጋውን ከነቫቱ መሙላት ይጠበቅባቸዋል። 
  • ስልክ ቀጥር፡- 0342407162/0919068385/0914830469 
  • ፋክስ ፡- 0344407309 

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን 

መቐለ ቅ/ፅ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo