የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ለ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ የቢሮ እቃዎች ግዥ ለመግዛት ህጋዊ ከሆኑ አቅራቢዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

አፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ /ቤት
  • ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ቀን : 7/9/2012
    ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን :  10 ቀናት እስከ ቀኑ 3:00
    ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን : 10 ቀናት እስከ ቀኑ 4:00
  • የቢሮ እቃዎች እና ሌሎች አላቂ እቃዎች
  1. 1. በዚህ ግልጽ ጨረታ የሚወዳደሩ አቅራቢ ድርጅቶች በ2011 ዓ.ም በጀት አመት የታደሰ የንግድ ፈቃድ ፤ የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና ምዝገባ ሠርተፍኬት ማቅረብ አለበት:
  2. 2. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የመወዳደሪያ ሀሳብ ኦርጅናሉን በአንድ ፖስታ ኮፒውን በአንድ ፖስታ የተጫራቾቹ ስምና ፊርማ አድራሻ በግልፅ ተፅፎባቸው ሁለቱም ፖስታዎች በአንድ ፖስታ ተደርጎ በሠም ታሽጎ በአፋር ብ/ክ/መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት በግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ ደጋፊ ስራ ሂደት ቢሮ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
  3. 3. የሚገዙት እቃዎችን አይነት እና ዝርዝር መግለጫ (Specification) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  4. 4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ/ ከፍለው ከአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት በግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ደጋፊ ስራ ሂደት ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡
  5. 5. የተዘጋጀው ጨረታ ዝርዝር ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ለተከታታይ 10 (አስር) ቀናት እስከ ከቀኑ 3፡00 ሰአት ድረስ ገዝተው በዛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰአት ተጫራቾች ባሉበት ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት በግዥና ፋይ/ንብ/አስተ/ደጋፊ ስራ ሂደት ቢሮ ይከፈታል፡፡
  6. 6. ተጫራቾች ሰነዱን ገዝተው በመሙላት እና በማዘጋጀት ኦሪጅናል የመወዳደሪያ ሀሳብ ዶክመንታችሁን በአንድ ፖስታ ውስጥ በሰም በማሸግ ኮፒውን በሌላ ፖስታ ውስጥ በሰም በማሸግ በማስገባት ሁለቱንም ፖስታዎች በአንድ ፖስታ አድርጎ በሰም አሽገው ለዚሁግዥ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  7. 7. ቢሮውሊገዛውያቀረበው የእቃ ዝርዝር ተጫራቾቹ ለሚሸጧቸው እቃዎች በእስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
  8. 8. ሻጭ ንብረቱን በንብረት ክፍል ድረስ ወስዶ ካስረከቡ በኋላ በስሙ ሞዴል 19 አስቆርጦ ሂሳብ ክፍል በመውሰድ ሂሳቡን ማወራረድ አለበት::
  9. 9. አሸናፊው ድርጅትያአሸነፈበትንእቃዎች ወይም አገልግሎቶች በራሱ ትራንስፖርት ቢሮአችን ድረስ ለንብረት ክፍል ማስረከብ አለባቸው
  10. 10. የጨረታው መክፈቻ ጊዜ እና ቀን የጨረታውን ፕሮግራም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙ ቢቀ የጨረታውን መክፈቻ ሂደት አያስተጓጉልም::
  11. 11. ቢሮው ጨረታውን የተሻለ አማራጭ ካገኘ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. 12. ማንኛውምየጨረታተወዳዳሪለሚያቀርቧቸው እቃዎች ብር 20,000.00/ሃያ ሺህ የጨረታማስከበሪያ CPOከመወዳደሪያ ሰነድ ማቅረቢያ ጋር በፖስታ ታሽጎ ማቅረብ አለበት፡፡

በተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለጎት በቢሮው ስልክ ቁጥር፡033-666-05-02 ደውለው ይጠይቁ፡፡

የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo