በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ከዚህ በታች የተረዘረዘሩትን ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ

1 የማሽነሪ መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የሎደር ጎማና ፣የግሬደር ካላማደሪ እና ፣የ ጀነሪተር መለዋወጫ ዕቃዎች

2 የግንባታ ዕቃዎች ፣የቧንቧ ዕቃዎችና ፣የኤለክትሪክ ዕቃዎች

3አላቂ  የፅህፈት መሳሪያዎች

4 የመሮጫ ማሽን

ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛዉም ህጋዊ ተጫራች በጨረታዉ መወዳደር ይችላል

1 ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸዉ የጨረታ ዓይነቶች ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸዉ በአቅራቢነት ስለመመዝገባቸዉ የአቅራቢነት ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና ግብር ስለመከፈላቸዉ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ

2 የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ /ከፋይነት/ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ

3 የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ

4 ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸዉ ለእያንዳንዱ ጨረታ የጨረታ ማስከበሪያ በጨረታ ሰነድ ላይ በተገለፀዉ መመሪያ መሰረት በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

5ተጫራቾች የሚጫረቱበት ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ የእቃዉን አይነት ኤንቨሎፕ ላይ በግልፅ መፃፍ ይኖርባቸዋል

6 የጨረታዉ ሰነድ ተጫራቾች ዝርዝር መመሪያ ጋር የማይመለስ ብር 100 በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታዉጆ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ባሉት የስራ ቀናት ዉስጥ ሽሬ በሚገኘዉ የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መመሪያ ግዠ ቡድን ቢሮ መግዛት ይቻላል

7ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸዉን ሽሬ ከተማ በሚገኘዉ ማ/ ዕዝ ጠ /መመሪየ መዝናኛ ክበብ ዉስጥ ለዚሁ በተዘጋጀዉ ሳጠነ ዉስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል

8 ጨረታዉ ጥር 27 ቀን 2008 ዓም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4 ፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ማ/ ዕዘ መዝናኛ ክበብ ዉስጥ ይከፈታል

9 አሸናፊ ተጫራቾች ዉል ሲፈፅሙ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል ያሸነፉበትን እቃ በራሳቸዉ ወጭ በማጋጋዝ ሽሬ ከተማ በሚገኘዉ የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መመሪይ ግምጃ ቤት ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል

10 መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ እንዲሁም ካጠቃላይ ግዠ 20 % ጨምሮ በኮንሶ የመግዛት መብቱ የተጠበቀ ነዉ

ለበለጠ መረጃ 0344442377 እና 0344444393 ይደዉሉልን

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo