በሃገር መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜን ዕዝ የ5ኛ ሜ/ድ ክ/ጦር መምሪያ በ2012 ዓ/ም በጀት ዓመት ለክ/ጦራችን ለተለያዩ ስራ አገልግሎት የሚውሉ የቀላል ተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎችን፤የህንፃ መሳሪያዎችን እና የቢሮ ማሽን መለዋወጫ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

በሰሜን ዕዝ የ5ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር መምሪያ
  • የቀላል ተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎችን፤
  • የህንፃ መሳሪያዎችን እና
  • የቢሮ ማሽን መለዋወጫ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች በሙሉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡ ተጫራቾች የማስረጃቸውን ፎቶ ኮፒ በማቅረብ የዕቃዎችን ዝርዝር የያዙ ሰነድ የማይመለስ ብር 50.00 (ሃምሳ ብር) በመክፈል ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት በ33ኛ ክ/ጦር ጎንደር አዘዞ ወ/ዊ ካምፕ ግዥ ከፍል ቢሮ እያቀረቡ መግዛት ይችላሉ፡፡ ተጫራቾች ለተሸናፊው ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበርያ ብር 5,000,00 (አምስት ብር) በባንክ በተረጋጠ cpo ወይም በካሽ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቾች የእያንዳንዱ የዕቃ ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ እስከ ግንቦት 4 ቀን 2012 / ከቀኑ 800 ሰዓት ድረስ ሰነዱን ከገዙበት ቢሮ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው :: ጨረታው 800 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ከቀኑ 815 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ33ኛ ክ/ጦ ወ/ዊ መዝናኛ ክበብ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ መስሪያ ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ 0930962249 /0913133315 /0915279453 ይደውሉ፡፡

በሃገር መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜን ዕዝ 5 / /ጦር መምሪያ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo