የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የተለያዩ ዕቃዎችና አገልግሎቶች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ
  • ሎት 1. ጋብዮን
  • ሎት 2  1.Crawler Buldozer /ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ/ 2. Hydraulic Excavator
  • ሎት 3. ፀረ ተባይ ኬሚካል
  • ሎት 4 የእንስሳት መድኃኒት
  • ሎት 5. የቢሮ መገልገያ እቃዎች/ ፈርኒቸር/
  • ሎት 6. የእርሻ መገልገያ መሳሪያዎች
  • ሎት 7. ኤሌክትሮኒክስ /IT/ እቃዎች/ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፤ በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ዶክመንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መወሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፤ በጨረታ ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል። የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የVat ሰርተፍኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (Tin) እና ያለፈው ወር ቫት (vat) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት፣
  • ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር ኣለባቸው፤
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዘብ በCPO አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤ 
  • ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፤
  • ጨረታው በ04/09/2012 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የመሰብሰብያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ 
  • ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- በስልክ ቁጥሮች 0344403663/ 0344404346 ወይም በፋክስ ቁጥር 0344409971/0344403663 መጠየቅ ይቻላል፡፡ 

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo