የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የኤሌክትሮኒክስ /IT/እቃዎች እና Supply, Instaliation, Testing and Commissioning of 25KW solar PV Plant በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ
  • ሎት1 . ኤሌክትሮኒክስ /IT/እቃዎች
  • ሎት2. Supply, Instaliation, Testing and Commissioning of 25KW solar PV Plant for Wereda T/Adyabo, Kebele Atsrega, Vilage Tabtay Atsrega,r (ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ) 

በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፤ በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ዶክመንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፤ በጨረታውን ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል። 

የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የVat ሰርተፍኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (Tin) እና ያለፈው ወር ቫት Vat) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት፣ ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው፤ . 

የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዘብ በCPO አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤ ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 15% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፤ 

ጨረታው 18/09/2012 ዓም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ 

-ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 

0344403663/ 0344404346 ወይም በፋክስ ቁጥር 0344409971/0344403663 መጠየቅ ይቻላል 

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo