ሕብረት ወታደራዊ ስታፍ ኮሌጅ አገልግሎት የሚዉሉ የተለያዩ የኤለክትሮኒክስ እና ፈርኒቸር አቃዎች ፣የመሃንዲስ /ሰርቨይ / መሣሪያዎእ ፣ የቢሮ መጋረጃ ጨርቆች ፣የሲቪል ሰራተኞች የደንብ ልብስ፣ የፅዳት እቃዎች እንዲሁም የግቢ ማስዋብ ሥራዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ለማሰራት ይፈልጋል ስለሆነም በጨረታ ለመሳትፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች

ህብረት ወታደራዊ ስታፍ ኮሌጅ
  1. ለወጣዉ ጨረታ  በዘርፉ የተሰማሩ መሆናቸዉ የሚገልፅ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ  ያላቸዉ የዘመኑን ግብር ስለመክፈላቸዉ ማስረጃ አያይዘዉ ማቅረበ የሚችሉ
  2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና መመዝገባቸዉን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ኮፒ አያይዘዉ ማቅረብ የሚችሉ
  3. የግብር ግዴታቸዉን የተወጡና የግብር ከፋይ ሰርትፍኬት ማስረጃ ኮፒ አያይዘዉ ማቅረብ የሚችሉ
  4. በመንግስ መሰራቤት ጨረታ እንዲሳተፉ ያልታገዱ እና በመንግስት ግዥ በግልፅ ጨረታ  አፈፃፀም መመሪያ መሰረት ለመወዳደር ብቁ የሆኑ
  5. ተጫራቾች ለጨረታዉ ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ  ለጨረታ ማስከበሪየ 2 % በ ሲፒኦ ማስያዝ የሚችሉ
  6.  አሸናፊ ተጫራቾች ዉሉን ሲፈፅሙ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና የሚዉል ማስከበሪያ ከዉሉ ጠቅላላ ዋጋ 10 % ማስያዝ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል

ከላይ ከተጠቀሱትን መስፈርቶች አማልተዉ ከመጫረቻ ሰነዳቸዉ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥር 23 ቀን 2008 ዓም ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 2 ፡30 እስከ ቀኑ 1 1፡ 00 ሰዓት ባለ ግዜ  ዉስጥ መቀለ ሕ/ወ/ስ/ኮ ግዥ  ዴስክ ቢሮ ቁጥር 32 እንዲሁም አዲስ ኣበባ (ጃልሜዳ)  መከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መስራቤት ዋና መምሪያ ግዥ ክፍል በመቅረብ  ለዚሁ ጨረታ በአማርኛ የተዘጋጀዉን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100 በመክፈል ገዝተዉ መወዳደር ይችላሉ

የጨረታ ሳጥን  የሚዘጋጀዉ በኮሌጁ ግዥ ዴስክ ቢሮ ቁጥር 32 ዉስጥ ብቻ ሲሆን የሰነድ ማስረከቢያ ጊዜም ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ወን አንስቶ እስከ መዝጊያ ዕለት ድረስ ይሆናል

ጨረታዉ ጥር 24 ቀን 2008 ዓም ከጠዋቱ  በ 3፡ 45 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ በ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉና የኮሌጁ ታዛቢዎች በተገኙበት በኮሌጁ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል ባይገኙም ሰነዱ የተማላ ከሆነ በሌሉበት ይከፈታል የጨረታ ሳጠን ከታሸገ ብኃላ ዘግይቶ የሚመጣ ሰነድ ተቀባይነት የለዉም

ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ እንድ አስፈላጊነቱ ጨረታዉ በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መበቱ የተጠበቀ ነዉ

ኣድራሻ :መቀለ  ከመቀለ ኑኒቨርሲቲ ዋና ግቢ አላፍ ብሎ ወደ ኩሓ በሚወስዱ አስፋልት መንግድ በስተግራ በኩል ያለዉ የኮሌጁ ሕንፃ

ስልክ ቅጥር 0344407064

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo