ሂወት እርሻ መካናይዜሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር በ2012/2 013 ዓ.ም ምርት ዘመን የተለያዩ ፀረ አረም ኬሚካል በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ሂወት እርሻ መካናይዜሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

ድርጅታችን ሂወት እርሻ መካናይዜሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር በ2012/2013 ዓም ምርት ዘመን የተለያዩ ፀረ አረም ኬሚካል ጅምላ ጨራሽ (Non selective Herbicide lit 12,000 ) 2.4 D Lit 1,200 ) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች የጨረታው ዝርዝር መመሪያ የማይመለስ ብር 200 በመክፈል ይህ ጨረታ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው የስራ ቀን ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ፊንፊኔ ህንፃ 6ተኛፎቅ ከሚገኘው የኩባንያው ግዢና ጉዳይ ፈፃሚ ፅህፈት ቤት ወይም ሁመራ ከተማ ቀበሌ 04 ከሚገኘው የኩባንያችን ዋና ቢሮ ሰነዱን መወሰድ ይችላሉ። ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 11ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 400 ሰዓት ጨረታው ተዘግቶ በዕለቱ 430 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ድርጅታችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ

ስልክ ቁጥር 0911-2372 45 /0935406182 ደውለው ይጠይቁ፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo